Get Mystery Box with random crypto!

#አየር_ኃይል በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ አየር ኃይል በአውሮፕላን ቴክኒሻንነት ሙያ ፍላ | Ethio Job Vacancy

#አየር_ኃይል

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ አየር ኃይል በአውሮፕላን ቴክኒሻንነት ሙያ ፍላጎት ያላቸውን ወጣቶች ለማሰልጠን ዛሬ ይፋዊ ጥሪ አቅርቧል።

አየር ኃይል ፤ የአውሮፕላን ቴኪኒሻንነትን ሙያ መሰልጠን የሚፈልጉ ወጣቶች የወጡትን መስፈርቶች ሊያሟሉ እንደሚገባ አመልክቷል።

ከመስፈርቶቹ አንዱ የሆነው " የትምህርትና ሌሎች መመዘኛ " ሲሆን በዚህም በአየር ኃይል በአውሮፕላን ቴክኒሻንነት ለመሰልጠን ፦

- የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የሆኑ በሂሳብ ፣ ፊዚክስ ፣ እንግሊዘኛ ትምህርቶች አማካኝ ውጤህ ከ50% እና ከዚያ በላይ ያላቸው ሊሆኑ ይገባል።

- በ2013 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና አጠቃላይ ውጤት 300 እና ከዚያ በላይ ያላቸው መሆን አለባቸው።

- በ2014 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ደግሞ አጠቃላይ ውጤት 250 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ አለባቸው።

አየር ኃይል የሚያመለክቱ ወጣቶች የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱበትን ኦርጂናል ሰርተፊኬት እንዲሁም የኮሌጅ / ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከሆኑ ከሚማሩበት ተቋም የመጨረሻ አመት የውጤት ሪፖርት ማቅረብ አለባቸው ብሏል።

ከዚህ ባለፈ አየር ኃይል አካዳሚ የሚቀበላቸው በራሱ በአካዳሚው የሚሰጠውን #የመግቢያ_ፈተና ማለፍ የሚችሉትን እንደሆነ ገልጿል።

የምዝገባው ቦታዎች ከላይ ተያይዟል ።

የምዝገባው ቀን ከመጋቢት 18 ቀን 2015 ዓ/ም እስከ መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ/ም ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት እንደሆነ አየር ኃይል አሳውቋል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

@ethio_job_vacancy
@ethio_job_vacancy