#አየር_ኃይል በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ አየር ኃይል በአውሮፕላን ቴክኒሻንነት ሙያ ፍላጎት ያላቸውን ወጣቶች ለማሰልጠን ዛሬ ይፋዊ ጥሪ አቅርቧል። አየር ኃይል ፤ የአውሮፕላን ቴኪኒሻንነትን ሙያ መሰልጠን የሚፈልጉ ወጣቶች የወጡትን መስፈርቶች ሊያሟሉ እንደሚገባ አመልክቷል። ከመስፈርቶቹ አንዱ የሆነው " የትምህርትና ሌሎች መመዘኛ " ሲሆን በዚህም በአየር ኃይል በአውሮፕላን ቴክኒሻንነት ለመሰልጠን ፦ - የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪ የሆኑ በሂሳብ ፣ ፊዚክስ ፣ እንግሊዘኛ ትምህርቶች አማካኝ ውጤህ ከ50% እና ከዚያ በላይ ያላቸው ሊሆኑ ይገባል። - በ2013 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና አጠቃላይ ውጤት 300 እና ከዚያ በላይ ያላቸው መሆን አለባቸው። - በ2014 ዓ/ም ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ደግሞ አጠቃላይ ውጤት 250 እና ከዚያ በላይ ማስመዝገብ አለባቸው። አየር ኃይል የሚያመለክቱ ወጣቶች የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱበትን ኦርጂናል ሰርተፊኬት እንዲሁም የኮሌጅ / ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከሆኑ ከሚማሩበት ተቋም የመጨረሻ አመት የውጤት ሪፖርት ማቅረብ አለባቸው ብሏል። ከዚህ ባለፈ አየር ኃይል አካዳሚ የሚቀበላቸው በራሱ በአካዳሚው የሚሰጠውን #የመግቢያ_ፈተና ማለፍ የሚችሉትን እንደሆነ ገልጿል። የምዝገባው ቦታዎች ከላይ ተያይዟል ። የምዝገባው ቀን ከመጋቢት 18 ቀን 2015 ዓ/ም እስከ መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ/ም ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት እንደሆነ አየር ኃይል አሳውቋል። (ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል) @ethio_job_vacancy @ethio_job_vacancy 233 viewsedited 08:55