[ Album ] #MekdelaAmbaUniversity መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ፕሬዝዳንት አወዳድሮ ለመቅጠር የቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል። የሥራ መደብ ➧ ፕሬዝዳንት (የዩኒቨርሲቲውን ሥራዎችን በኃላፊነት ይሰራል፣ይመራል) የትምህርት ደረጃ ➧ 3ኛ ዲግሪ ወይም 2ኛ ዲግሪ እና ቢያንስ ረዳት ፕሮፌሰር ማዕረግ የሥራ ልምድ ➧ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወይም በሌላ መስክ ለሥራ መደቡ አግባብነት ባለው የተረጋገጠ የአመራርነት፣ የኃላፊነት እንዲሁም የምርምርና የማስተማር ልምድ ያለው/ያላት አጭር ስትራቴጂክ ፕላን ➧ አመልካቾች የሚወዳደሩበትን ዘርፍ ዋና ተግባር ለማሳደግና ለማሻሻል ስለሚከተሉት ስልት ከ10 ገጽ ያልበሰ አጭር መግለጫ በፅሁፍ ያቀርባሉ የሥራ ዘመን ➧ በውድድሩ የላቀ ውጤት በማምጣት የተመረጠው/ችው አመልካች በፕሬዝዳንትነት ለስድስት ዓመታት የሚሾም/የምትሾም ይሆናል አመልካቾች CV፣ የትምህርትና የሥራ ልምድ እና ሌሎች ማስረጃዎችን ዋናውን ከአንድ ጉርድ ፎቶግራፍ እንዲሁም 10 ገፅ አጭር መግለጫ በመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ ጽ/ቤት ወይም ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ መመዝገብ ወይም በኢሜይል መላክ ይችላሉ፡፡ የማመልከቻ ጊዜው የፊታችን አርብ መጋቢት 08/2015 ዓ.ም ያበቃል፡፡ ለተጨማሪ መረጃ፡- +251914074314 / +251914060672 (ሙሉ የማስታወቂያው መልዕክት ከላይ ተያይዟል፡፡) @ethio_job_vacancy @ethio_job_vacancy 2.1K views12:38