Get Mystery Box with random crypto!

ኢትዮ ቴሌኮም የመጨረሻውን ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ ይፋ አደረገ:: አፍሪ ኸልዝ ቲቪ ግንቦት 01 | Afrihealth TV

ኢትዮ ቴሌኮም የመጨረሻውን ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ ይፋ አደረገ::

አፍሪ ኸልዝ ቲቪ ግንቦት 01/09/2014 ኢትዮ ቴሌኮም የመጨረሻውን ትውልድ (5G) ቴክኖሎጂ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ ይፋ አድርጓል::

በአሁኑ ሰዐት በሸራተን አዲስ ሆቴል ይፋ እየተደረገ የሚገኘው ይህ የሞባይል ቴክኖሎጂ በአለም 70 ሀገራት በአፍሪካ ደግሞ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ6 ሀገራት ተግባራዊ መደረጉን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሪት ፍሬ ህይወት ታምሩ ተናግረዋል::

በቀጣይ 12 ወራትም 150 አካባቢዎች የዚህ ቴክኖሎጂ ተጠቃሚ እንደሚሆኑም ስራ አስፈፃሚዋ አክለዋል::

5G ቴክኖሎጂ ማስጀመሪያ ስነ ስርዐቱ ላይ በርካታ ሚኒስትሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል::
ዘጋቢ : አክረም ኑርያ