Get Mystery Box with random crypto!

Afrihealth TV

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_fun — Afrihealth TV A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_fun — Afrihealth TV
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_fun
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.78K
የሰርጥ መግለጫ

Afri Health has a vision to create awareness, transfer knowledge/skill on preventive health and empower the community to manage their health status.

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-07 07:55:51
በኮሎምቢያ ካሊ ከኦገስት 01-06/2022 ላለፋት ስድስት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ በሰነበተው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ19 አትሌቶች በሁለቱም ፆታ በ10 የውድድር ተግባራት ብቻ የተሳተፈው የአትሌቲክስ ቡድናችን በ6ወርቅ፣ በ5ብር እና 1የነሃስ በድምሩ በ12 ሜዳልያዎች ከዓለም ሃገራት አሜሪካንን እና ጃማይካን ተከትለን አትሌቶቻች ባደረጉት እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ 3ኛ ደረጃን ይዘን አጠናቀናል። ይህም ውጤት እስከ ዛሬ ከተካሄዱት የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተሳትፎ ታሪካችን ዘንድሮ የተመዘገበው ውጤት ከፍተኛው ሲሆን ከተሳተፍንበት ውስን የውድድር ተግባራት አንፃር እጅግ የሚያኮራ ውጤት ነው።



1.2K views04:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-05 20:14:02
ኢትዮ ቴሌኮም ከዳሽን ባንክ ጋር በመተባበር ሶስት የተለያዩ የቴሌ ብር የፋይናንስ አገልግሎቶችን ይፋ አደረገ።

ኢትዮ ቴሌኮም ከአንድ አመት በፊት ይፋ ባደረገው የቴሌ ብር የፋይናንስ አገልግሎት ከ22 ሚሊየን በላይ ደንበኞችን ማፍራት መቻሉን እንዲሁም በአሁኑ ወቅት ከ55 በላይ ተቋማት ጋር ቴሌ ብር እየሰራ እንደሚገኝ ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ፍሬ ህይወት ታምሩ አስታውቀዋል።

ዛሬ ይፋ የተደረጉት የፋይናንስ አገልግሎቶች ሶስት ሲሆኑ እነዚህም፦ቴሌ ብር እንደ ኪሴ፣ቴሌ ብር መላ እና ቴሌ ብር ሳንዱቅ/ቁጠባ ናቸው።

ቴሌ ብር መላ/ብድር፦ ለግለሰብ እስከ 10,000 ብር ለተቋማት ደግሞ እስከ 100,000 ሺህ ብር የብድር አገልግሎት ይሰጣል።

ቴሌ ብር እንደ ኪሴ፦ በቴሌ ብር አማካኝነት ግብይት ሲፈፀም የጎደለ የገንዘብ መጠን ካለ እስከ 2,000 ብር የብድር አገልግሎት ይሰጣል።

ቴሌ ብር ሳንዱቅ/ቁጠባ፦ ከትንንሽ ገንዘቦች ጀምሮ መቆጠብ የሚያስችል የፋይናንስ አገልግሎት።

ብድሩ በዳሽን ባንክ ወጪ የሚደረግ ሲሆን ሲስተሙ ደግሞ በኢትዮ ቴሌኮም የሚመራ መሆኑ ነው የተገለፀው።

የዚህ የፋይናንስ አገልግሎት ለማስጀመር ያስፈለገበት ምክንያት በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚኖሩ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሆነ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬ ህይወት ታምሩ አስታውቀዋል።
1.2K views17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 22:17:46
የኢትዮጵያ እግር ኴስ ፌዴሬሽ ምርጫ ዕጩዎች
1.3K views19:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 12:52:32
የቀጣይ ዓመቱ የኢትዮጵያ ቤት ኪንግ ፕሪምየር ሊግ የጨዋታ መርሃ ግብር ይፋ ሆነ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማህበር የ2015 የጨዋታ መርሃ ግብርን ዛሬ ረፋድ በጽህፈት ቤቱ አውጥቷል፡፡ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ከመውረድ የተረፉ 13 ክለቦችና ከከፍተኛ ሊግ ወደ ፕሪምየር ሊጉ ያደጉት ለገጣፎ ለገዳዲ፣ ኢትዮጵያ መድህንና ኢትዮ ኤሌክትሪክን አካቶ የ16ቱን ክለቦችን የጨዋታ መርሃ ግብር ዛሬ አውጥቷል፡፡
መስከረም 20 2015 የቀጣይ ዓመቱ የፕሪምየር ሊግ መርሃ ግብር ይጀመራል ያለው አክሲዮን ማህበሩ የመጀመሪያ ዙር የ15 ሳምንት ጨዋታዎቹን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህ መሰረት በአንደኛ ሳምንት ባህርዳር ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ፣ ወላይታ ድቻ ከኢትዮጵያ ቡና፣ ፋሲል ከነማ ከአዳማ ከተማ፣ወልቂጤ ከተማ ከአርባ ምንጭ ከተማ፣ ሃዋሳ ከተማ ለገጣፎ ለገዳዲ፣ መቻል ከሃድያ ሆሳዕና፣ ኢትዮጵያ መድህን ከቅዱስ ጊዮርጊስና ድሬደዋ ከተማ ከሲዳማ ቡና እንደሚጫወቱ የወጣው ድልድል ይጠቁማል፡፡

በመጀመሪያ ዙር ከሚጠበቁ ጨዋታዎች መካከል በአምስተኛ ሳምንት በሸገር ደርቢ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ቡና 6ኛ ሳምንት ፋሲል ከነማ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የ2014 የኢትዮጵያ ቤት ኪንግ ፕሪምየር ሊግ ሳይቆራረጥ መካሄዱን በጥንካሬ በየቀኑ ሶስት ጨዋታዎች ማካሄድን በድክመት ያነሱት የአክሲዮን ማህበሩ የውድድርና ስነ ስርዓት ኮሚቴ ሰብሳቢው ዶክተር ወገኔ ዋልተንጉስ ናቸው፡፡

የ2015 የውድድር መርሃ ግብር ካለፉ ስህተቶች ትምህርት የሚቀሰምበት ነው ያሉት ሰብሳቢው ለተግባራዊነቱ ከወዲሁ በቂ ዝግጅት ይደረጋል ብለዋል፡፡
1.5K views09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 06:56:10
በኮሎምቢያ ካሊ የአለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና የ5000ሜ. የወንዶች የፍፃሜ ውድድር

አዲሱ ይሁኔ በ14:03.05 በሆነ ሰዓት 1ኛ
ገበየሁ በላይ በ14:04.55 በሆነ ሰዓት 4ኛ ዲፕሎማ

እንኳን ደስ አለን!
1.2K views03:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 18:32:20 ሰኔ 03 2014 - የስፖርት አበይት መረጃዎች
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ወደ ሐገር ቤት ለመመለስ ጉዞ ሲጀምር በአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው ልዑክም ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ ነው፡፡
ለቀጣይ ዓመቱ የአፍሪካ ዋንጫ በምድብ አራት ከግብጽ፣ ማላዊና ጊና ጋር የተደለደለው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የምድቡን ሁለተኛ ጨዋታ ከግብጽ ጋር አድርጎ 2ለ0 ማሸነፉ ይታወቃል፡፡ ሳይገመት ከጨዋታ ብልጫ ጋር ያሸነፈው ብሄራዊ ቡድኑ በማላዊ ከተዘጋጀለት የምሳ ግብዣ በኋላ ከደቂቃዎች በፊት ወደ አዲስ አበባ ጉዞ መጀመሩን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ተናግሯል፡፡
ፈርዖኖቹን ላሸነፉት የዋልያዎቹ አባላት 2 ሚሊዮን ብር ሽልማት እንደሚሰጥ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መናገሩ ይታወሳል፡፡ ወደ አዲስ አበባ ጉዞ በጀመረው ስብስብ ውስጥ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጅራና ዋና ጸሐፊው ባህሩ ጥላሁንም እንዳሉበት ታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በቀጣዩ መስከረም ወር ከጊኒ ጋር የምድቡን ሶስተኛ ጨዋታ የሚያከናውን ይሆናል፡፡ ብሄራዊ ቡድኑ ግብጽን አሸንፎ ከፍተኛ ሙገሳ ቢቀርብለትም ዓለም ዓቀፍ ጨዋታዎችን የሚጫወትበት ሜዳ ማጣቱ የመንግስት ቀጣዩ የቤት ስራ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
በተያያዘ ዜና በሞሪሺየስ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ አትሌቶች አመርቂ ውጤት እያስመዘገቡ ነው፡፡ ከሰዓታት በፊት በተካሄደ የ3 ሺ ሜትር መሰናክል ኢትዮጵያውያን ተከታትለው በመግባት ማሸነፋቸው ታውቋል፡፡
ርቀቱን በ8 ደቂቃ ከ27 ሰከንድ ከ38 ሰከንድ ያጠናቀቀው ኃይለማሪያም አማረ ወርቅ ሲወስድ ታደሰ ታከለ የብር ሜዳሊያውን አግኝቷል፡፡ ሳሙኤል ፍሬው ደግሞ አምስተኛ ደረጃን አግኝቷል፡፡ በ10 ሺ ሜትር ሞገስ ጥዑማይና ጭምዴሳ ደበሌ የወርቅና ብር ሜዳሊያ ማግኘታቸው ይታወሳል፡፡ በ5 ሺ ሜትር ሴቶች ፋንታዬ በላይነህ ብር እነዲሁም በ1 ሺ 500 ሜትር ሴቶች አያል ዳኛቸው የነሀስ ሜዳሊያ ማግኘታቸው አይዘነጋም፡፡
ከትናንት በስቲያ ረቡዕ የተጀመረው 22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከነገ በስቲያ እሁድ ይጠናቀቃል፡፡ ኢትዮጵያ ዛሬና ነገ ተጨማሪ ሜዳሊያዎችን እንደምታገኝ ይጠበቃል፡፡
ከውጭ
ከዛሬ አርብ ጀምሮ በተከፈተው የክረምቱ የዝውውር መስኮት የበርካታ ተጨዋቸች እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡
የዝውውር መስኮቱ ሳይከፈት ፊሊፕ ኩቲኖን፣ ቡበከር ካማራን፣ ዲየጎ ካርሎስን እና ሮቢን ኦልሰን ያስፈረመው አስቴንቪላ ስምምነቱን ዛሬ ያጸድቃል፡፡ ማንችስተር ሲቲም የኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ ስምምነቱን የሚያጸድቀው ከዛሬ ጀምሮ ነው፡፡
ሪያል ማድሪድ የአንቶኒዮ ሩዲገርን ሊዮን የአሌክዛንደር ላካዜት የነጻ ዝውውርን በይፋ የሚያጸድቁበት ጊዜ ላይ ደርደዋል፡፡ የፖል ፖግባ፣ ጋሬዝ ቤል፣ የሴ ሊንጋርድ፣ ሳዲዮ ማኔ፣ ዳርዊን ኑኔዝ፣ሮበርት ሎዋንዶውስኪ፣ ኡስማን ደምበሌ፣ የክሪስቶፈር ንኩንኩ፣ የዝውውር አጀንዳም የሚዘጋው ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ወራት ገደማ ክፍት ሆኖ በሚቆየው የክረምቱ የተጨዋቾች የዝውውር ወቅት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
310 views15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 18:32:13
259 views15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 11:27:21

403 views08:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 21:11:43
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የግብጽ አቻውን 2 ለ 0 አሸነፈ

ዛሬ ምሽት በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የግብፅ አቻውን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።

በማላዊ ቢንጉ ብሔራዊ ስታዲየም እየተካሄደ ባለው የ2023 የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታ ለዋሊያዎቹ ዳዋ ሆቴሳ በ21ኛው ደቂቃ እና ሽመልስ በቀለ በ40ኛው ደቂቃ ጎሎቹን አስቆጥረዋል።
269 views18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 12:07:12

356 views09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ