Get Mystery Box with random crypto!

🇨🇬 ደጉ ሳምራዊ (ኢትዮጵና ቅድስት ቤተክርስቲያን )

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_betecrstian — 🇨🇬 ደጉ ሳምራዊ (ኢትዮጵና ቅድስት ቤተክርስቲያን )
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethio_betecrstian — 🇨🇬 ደጉ ሳምራዊ (ኢትዮጵና ቅድስት ቤተክርስቲያን )
የሰርጥ አድራሻ: @ethio_betecrstian
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.62K
የሰርጥ መግለጫ

#ደጉ_ሳምራዊ
የተገፊዎች ድምፅ ነው!!!
-ህዳር 2-2013 ዓ.ም
@Ethio_Betecrstian
ለአስተያየትዎ ➧➧ @gebretsadik24_bot ላይ ቢጽፉልን ከእኛ ጋር ይደረሳል።

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-12-11 18:27:56 ወዲያው ግን ያቺ በትር እባብ ሁና ሽፍቶችን አጥፍታቸዋለች:: ጻድቁ ለቤተሰብ እየታዘዙ: ንጽሕናቸውንም እየጠበቁ ኑረው 30 ዓመት ሲሞላቸው ወላጆቻቸው ግድ ብለው ማርያም ክብራ ለምትባል ወጣት አጯቸው::

እሳቸው ግን በሠርጉ ሌሊት ከጫጉላ ቤት ጠፍተው በርሃ ገቡ:: ከዚያም በቅዱስ መልአክ መሪነት ሃገረ ምሑር ደረሱ:: በቦታውም ጣዖትን ሰባብረው: ተአምራትንም አድርገው: ሕዝቡን ወደ ክርስትና መለሱ:: መስፍኑ አውጊት ግን ተፈታተናቸው: አሠራቸው: አሥራባቸው::

በጦር እወጋለሁ ሲል ግን መሬት ተከፍታ ከነ ተከታዮቹ ውጣዋለች:: ከ5 ዓመታት በኋላ ግን ማልደው: ከሰጠመበት አውጥተው አጥምቀውታል:: ቀጥለውም ምድረ ጉራጌ ወርደው: ሕዝቡን አሳምነው አጥምቀዋል::

የአዳልን ሕዝብና ንጉሡን አብደልማልን አስተምረው ያጠመቁም እርሳቸው ናቸው:: ድል አሰግድ የሚባለውን መስፍንም ያሳምኑ ዘንድ ጠንቅዋዮቹን ድል አድርገው አጥፍተዋል::

ጻድቁ ዜና ማርቆስ ከዚህ ሐዋርያዊ ሥራቸው በተጨማሪ በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ምንኩስናን ከተቀበሉባት ቀን ጀምረው በጾም: በጸሎትና በሰጊድ ኑረዋል:: ፀሐይን በምድረ ጉራጌ እስከ ማቆም ደርሰውም ብዙ ተአምራትን ሠርተዋል::

አእላፍ ደቀ መዛሙርትን ሲያፈሩ 200 አንበሶች በቀኝ: 200 ነብሮች በግራ ይከተሏቸው ነበር:: ደብረ ብሥራትን ጨምሮም ገዳማትን አንጸዋል:: በመጨረሻም የምሕረት ቃል ኪዳንን ከፈጣሪ ዘንድ ተቀብለው ታኅሣሥ ሦስት ቀን በ140 ዓመታቸው ዐርፈዋል::

††† የእመቤታችን ድንግል ማርያም ጣዕሟ: ፍቅሯ: ጸጋዋና በረከቷ ይደርብን::

††† ታኅሣሥ 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም
2.ብጹዓን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱሳን ካህናት ዘካርያስና ስምዖን
4.ቅዱስ ፋኑኤል ሊቀ መላእክት
5.አቡነ ዜና ማርቆስ ጻድቅ

††† ወርኀዊ በዓላት
1.አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ጻድቅ (ዘደብረ በንኮል)
2.አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
3.ቅዱስ ቄርሎስ ሊቅ (ዓምደ ሃይማኖት)

††† "ድንግል ሆይ! አንገታቸውን እንደሚያረዝሙ እንደ እብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለሽም:: በቅድስናና በንጽሕና በቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ::
ድንግል ሆይ! ምድራዊ ሕብስትን የተመገብሽ አይደለም:: ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ሕብስትን እንጂ::
ድንግል ሆይ! ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለም:: ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥን እንጂ::" †††
(ቅዳሴ ማርያም)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††
70 views15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-11 18:27:55 የዲ/ዮርዳኖስ አበበ ትምህርቶች የሚተላለፉበት ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት:
††† እንኳን ለእግዝእትነ ማርያም (#በዓታ): አቡነ ዜና ማርቆስ ጻድቅ እና ቅዱስ ፋኑኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም †††

††† ከነገደ ይሁዳ የሚወለድ ቅዱስ ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ ሌዊ (አሮን) የተወለደች ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች "ልጅ የላችሁም" በሚል ይናቁ ነበር::

ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት የአብርሃምና ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም::

የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን እርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች ቅድስት ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: "እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን ሳይቀር በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች::

ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለ40 ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በ40ኛው ቀን ሁለቱም ሕልምን ያልማሉ::
እርሱ:-
*ነጭ ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጀሮ ገብታ: በማሕጸኗ ስትደርስ አየ::

እርሷ ደግሞ:-
*የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለ7 ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ::

በ7ኛው ቀን (ማለትም ነሐሴ 7) መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ::

እንደ ሥርዓቱም አብረው አድረው እመ ብርሃን ተጸነሰች::
"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ . . .
ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: (ቅዳሴ ማርያም)

††† "ለጽንሰትኪ በከርሥ::
እንበለ አበሳ ወርኩስ::
ወለልደትኪ እማሕጸን ቅዱስ . . ."
"ድንግል ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል (ያለ ጥፋት) ነው: የተወለድሽበት ማሕጸንም ቅዱስ ነው . . ." (መጽሐፈ ሰዓታት፣ ኢሳ. 1:9)
"ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ::
ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ::"
"ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን::
ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አወጣችልን (ወለደች-አስገኘችልን)"

የዓለማችን ወላጆች ነቢያት ሐዋርያትን: ጻድቃን ሰማዕታትን ወልደው ከብረዋል: ተመስግነዋል:: ኢያቄምና ሐና ግን ፍጥረት ሁሉ በአንድነት ቢሰበሰብ በእግሯ የረገጠችውን ትቢያ እንኳ መሆን የማይችል: የሰማይና የምድር ንግሥት: የእግዚአብሔርን እናት: እመቤታችን ማርያምን ወለዱልን::

ኢያቄም ወሐና ለእግዚአብሔር የሥጋዌ አያቶቹም ተባሉ:: ቅዱሳኑ እስኪያረጁ ድረስ በመካንነት አዝነው ፀልየዋል:: ንጽሕናቸውና ደግነታቸው ተመስክሮላቸው ድንግል ማርያምን አግኝተዋል::

እመቤታችን ነሐሴ 7 ቀን ተጸንሳ ግንቦት አንድ ቀን ተወልዳለች:: ከአዳም ስሕተት በኋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተወለደች የመጀመሪያዋ ሰው ድንግል ማርያም ሆናለች:: (ኢሳ. 1:9)

††† የእመቤታችን የዘር ሐረግ:-
*አዳም-ኖኅ-አብርሃም-ይስሐቅ-ያዕቆብ=
*በእናቷ:-
ሌዊ-ቀዓት-እንበረም-አሮን-ቴክታና በጥሪቃ-ሔኤሜን-ዴርዴን-ቶና-ሲካር-ሔርሜላና ማጣት-ሐና::

*በአባቷ በኩል:-
ይሁዳ-ፋሬስ-ሰልሞን-ቦኤዝ-እሴይ-ዳዊት-ሰሎሞን-ሕዝቅያስ-ዘሩባቤል-አልዓዛር-ቅስራ-ኢያቄም ይሆናል::

ለጨለማው ዓለም የብርሃን መቅረዝ ሆና ትጠቅመን ዘንድ: አንድም ትንቢቱና ምሳሌው ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም: በሊባኖስ ተራራ ከ2,023 ዓመታት በፊት ተወልዳለች::

ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና ድንግል እመ ብርሃንን ከወለዱ በኋላ ለ3 ዓመታት እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑ: ነዳያንንም ሲጠግኑ ኖሩ:: በእነዚህ ዓመታትም ቅድስት ሐና ድንግል ማርያምን ከእቅፏ አውርዳት አታውቅም::

ቅዱሳን መላእክትም ዘወትር እየመጡ ያጫውቷት ይንከባከቧትም ነበር:: 3 ዓመት በሞላት ጊዜም በቅድስት ሐና አሳሳቢነት ብጽዓታቸውን (ስዕለታቸውን) ይፈጽሙ ዘንድ ተዘጋጁ::

እንደ ሥርዓቱ የሚዘጋጀውን (መባውን) ይዘው ወደ ቤተ መቅደስ ሲደርሱ አበው ካህናትና የመቅደሱ አገልጋዮች ሁሉ ሊቀበሏቸው ወጡ:: ሕዝቡ: ሊቃነ ካህናት ቅዱሳን ዘካርያስና ስምዖን: ኢያቄም ወሐና ከድንግል ማርያም ጋር ቆመው ሳሉም ሊቀ መላእክት ፋኑኤል ከሰማይ ወርዶ ረቦ ታየ::

ከቅዱስ ዘካርያስ ጀምሮ ሁሉም ሰው ሕብስትና ጽዋዑን ለመቀበል ቀረበ:: ግን መልአኩ ራቀ:: ድንግል ማርያም በቀረበች ጊዜ ግን ከመሬት አፈፍ አድርጐ አንስቶ: ክንፉን ጋርዶ ሰማያዊውን ማዕድ መገባት:: በዚህ ደስ የተሰኙ ካህናትና ሕዝቡ እየዘመሩ በታኅሣሥ ሦስት ቀን ወደ ቤተ መቅደስ አስገብተዋታል::

አማናዊት መቅደሰ መለኮት ድንግል ማርያም ወደ ኦሪቱ ቤተ መቅደስ በገባችበት ዕለት ጸሎታችን እንድትሰማን እንደ ሊቃውንቱ:-
"ማርያም አንቲ ሰዋስው ዘምድረ ሎዛ::
ዲቤኪ ትዕርግ ጸሎትየ ከመ ጼና ሠናይ መዓዛ::
ኀበ ለነፍስየ ታሰስል ትካዛ" እንላለን:: (አርኬ)

††† አቡነ ዜና ማርቆስ ጻድቅ †††

††† አባ ዜና ማርቆስ በሃገራችን በተለይ በደቡብ ምድረ ጉራጌ ስመ ጥር ሐዋርያዊ ጻድቅ ናቸው:: ምድረ ሽዋ ደግሞ እርሳቸውን ጨምሮ የብዙ ቅዱሳን መፍለቂያ ናትና ክብር ይገባታል:: ነቢየ ጽድቅ ዳዊት "ትውልደ ጻድቃን ይትባረኩ-የጻድቃን (የቅኖች) ትውልድ ይባረካል" (መዝ. 111) ያለው ነገር በምድረ ዞረሬ (ጽላልሽ) ተፈጽሟል::

ሦስት ወንድማማች የተባረኩ ካህናት በስፍራው ነበሩ:: ስማቸው ጸጋ ዘአብ: እንድርያስና ዮሐንስ ይባላል:: ከእነዚህ መካከልም ጸጋ ዘአብ: እግዚእ ኃረያን አግብቶ ኮከበ ከዋክብት ተክለ ሃይማኖትን ሲወልድ ካህኑ ዮሐንስ ደግሞ ዲቦራ የምትባል ደግ ሴት አግብቶ ዜና ማርቆስን ወልዷል::

የአቡነ ዜና ማርቆስ ጽንሰታቸው ሚያዝያ 30 በብሥራተ ማርቆስ ወንጌላዊ ሲሆን ልደታቸው ደግሞ ኅዳር 24 ቀን በበዓለ ሱራፌል ካህናተ ሰማይ ነው:: ዘመኑም 13ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው::

ዜና ማርቆስ በተወለዱ በ40 ቀናቸው አጐታቸው ቀሲስ እንድርያስ (የ72 ዓመት ሽማግሌ ናቸው) ሊያጠምቁ ቀረቡ:: ሕጻኑ ዜና ማርቆስ ግን ከእናታቸው እቅፍ ወርደው 3 ጊዜ "እሰግድ ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ" እያሉ ቢሰግዱ የመጠመቂያው ገንዳ ውኃ ፈላ::

ይህንን የተመለከቱት ካህኑ ደንግጠው ወጥተው ሲሮጡ ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት ተገልጦ "አትፍራ! ይልቁኑ ከጠበሉ ራስህን ተቀባ" አላቸው:: እንዳላቸው ቢያደርጉ ራሰ በራ ነበሩና ጸጉር በቀለላቸው::

ሕጻኑ ዜና ማርቆስ ግን 5 ዓመት ሲሞላቸው ወደ ጉባኤ ቤት ገብተው በአጭር ጊዜ ብሉይ ከሐዲስ ጠነቀቁ:: ዲቁናን ተቀብለው ወደ ቤታቸው ሲመለሱም ሽፍቶች አግኝተው: በትራቸውን ቀምተው: አንገላተው ሰደዋቸዋል::
61 views15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 14:57:10
ያዕቆብ 5:17
ÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻ
ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥
ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች።
164 views11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 10:43:03 #ይቺ ናት ኢትዮጵያ

የዘር ፓለቲካ ዘልቆ የሚታይባት ወንድማማችነታችን ተረስቶ ከአንድ እናት ሀገር ኢትዮጵያ መፈጠራችንን እረስተን ፣ፈርሀ እግዚአብሔርን ዘንግተን መገዳደላችንን ቀጥለናል አሁንም አለን ።በዚሁ ከቀጠልን ግን ኢትዮጵያስ የምትባል ሀገር ትኖር ይሆን ?

መቼ ይሆን ግን ማብቂያው ?
መፅሐፍ አገብጬ ፣አባቶቼን ጠይቄ፣ ጎግል ጎልጉዬ ...መልስ ያጣሁለት ጥያቄ ነው ።
መቼ ነው ፖለቲከኞች ህዝባቸውን ለእኩይ ተግባር መጠቀማቸውን የሚያቆሙት ? መቼ ነው የነሱን ልጅ በሞቀ ቤት በአውሮፓ እና አሜሪካ አስቀምጦ እዚህ ያለውን ባዶ ሆዱን የሚያድረውን ወጣት መጠቀሙን የሚያቆመው ? መቼ ነው አንድነታችን የሚመለሰው ? መቼ ነው ወጣቱ የእናትን ጓዳ ሊጥ መድፋት ትቶ ለእናቱ ንፁህ እንጀራ የሚያመጣው ? መቼ ነው ...? መቼ ነው ....? መልስ ያላገኘሁላቸው ጥያቄዎች ።

አስታውሳለሁ በአንድ ወቅት የአማርኛ ቋንቋ መምህራችን እንዲህ ብላን ነበር ''አንድ አዛውንት ሲሞት አንድ ቤተመፃህፍት እንደተቃጠለ ይቆጠራል'' ... እና እስካሁን ስንት ቤተመፃህፍት ፣ስንት የእውቀት አባቶችን አተን ይሆን ?

ከሀገራችን ሰንደቅዓላማ ይልቅ ሰባራ ሰንደቅ ከልካይ ሳይኖራቸው ሲውለበለቡ አያለሁ ያሳዝናል ኢትዮጵያን መርሳታችን ያሳዝነኛል።
''እዛ ጋር ጤፍ ቆጠራ
እዚህ ጋር ቃል ምንዘራ
ሀገር ምድሩ ባንቺ እየተጠራ''

ስኬት ያለ ውድቀት ማግኘት እንደማይቻለው ይህም ግዜ አልፎ የኢትዮጵያን ትንሳኤ እንደምናይ እርግጠኛ ነኝ ምክንያቱም የንፁሀን ነፍስ ወደ ፈጣሪዋ አብዝታ ስለምትጮህ ሁሉም የዘራውን ያጭዳልና ።

''የአሜሪካው ከመጣ አለን መመለሻ
የሱዳኑ ቢመጣ አለን መመለሻ
እኛን ያስቸገረን ሀበሻ ላበሻ''

''ሰላም ፣አንድነት እና ፍቅር ቸሩ አምላካችን አብዝቶ እንዲያድለን ከልብ እመኛለሁ ።''

share and join
Ethio_Betecrstian
179 views07:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-09 12:47:18
@ጎንደር ደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያም ቤተክርስቲያን
።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብቸኛው የታች ቤት አቋቋም ምስክር ጉባኤ ቤት ያለባት ታላቅ ደብር ናት።

share And join
@Ethio_Betecrstian
206 views09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-09 08:37:37 “ በሕይወትህ በረከት እንዲከተልህ አመስጋኝ ሁን ! ”
. . .
በሕይወታችን ብዙ ልናሟላቸው የምንፈልጋቸው ነገሮች ይኖራሉ።
ጠቢቡ ሰለሞን በመጽሐፈ መክብብ 1:7 ላይ ሲናገር " ፈሳሾች ሁሉ ወደ ባሕሩ ይሄዳሉ ባሕሩ ግን አይሞላም " ይላል።
.
ይህም ምን ቢሰጠው የትኛውም ያህል ቢትረፈረፍለት የሰው ልጅ ምኞትና ፍላጎት ማለቂያ የለውምና። እኛም ገንዘብ፤ ስራ፤ ፍቅር፤ ዝና፤ ስልጣን፤ በምኞት ቋጠሯችን ውስጥ ካካበትናቸው ጥቂቶቹ ናቸው።
.
መመኘቱ ባልከፋ …..ነገር ግን ብዙዎቻችን የሌለንን ስንመለከት ያሉንን ነገሮች ዓይን እንነፍጋቸዋለን ስለዚህ መጠየቅ እንጂ ማመስገን ይሳነናል፤ በዚህም ሁልግዜ ጠያቂዎች እንጂ አመስጋኞች አይደለንም። ልብ በሉ ምኞቶቻችን ሁሉ ሊሳኩ የሚችሉት ባለን ነገሮች መጀመሪያ መደሰት እና ማመስገን ስንጀምር ነው።
.
ለምሳሌ፦ አንድ ወዳጃችን በችግራችን ደርሶ ረዳን እንበል፤ ላደረገልን እርዳታ ምስጋና ካልሰጠነው እንዴት ብሎ በሌላ ችግራችን ይደርስልናል?፤ አምላካችን እግዚአብሔርም ላደረገልን ነገር ባመሰገንነው ቁጥር ሌሎች ልመናችንን ሰምቶ በበረከት ላይ በረከት ያትረፈርፍልናል። ስለዚህ ሁልግዜ አመስጋኝ አንደበት ሊኖረን ይገባል።
.
ነገር ግን በምስጋና ፈንታ “በቂ ገንዘብ አላገኝም”፤ “ኑሮዬ ምስቅልቅሉ የወጣ ነው” ፤ “መልካም የትዳር አጋር አላገኘሁም”፤ “ስኬታማ አይደለሁም” " እግዚአብሔር አይሰማኝም" የምንልና የምንማረር ከሆነ ያለንን ነገሮች እንዳናይ ከማድረጋቸውም በላይ በረከታችንን የማራቅና ያለንም በረከት ልናጣና ልንነጠቅ እንችላለን። ብዙዎቻችን ግን ይህንን አንረዳም።
ለደቂቃ ልቦናችንን ሰብስበን ካስተዋልነው እያንዳንዶቻችን በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ብንሆን እንኳን፤ ልናመሰግን የምንችልበት ብዙ ምክንያቶች አሉን። እንደው ዋጋቸውን እያራከስን ነው እንጂ እያንዳንዶቻችን ሌሎች የሚመኟቸው ነገሮች እኛ ጋር ዋጋ አጥተው ተቀምጠዋል።
.
ለምሳሌ፦ የአልጋ ቁራኛ የሆነ ሰው በህይወቱ የሚመኘው ነገር ሙሉ ጤንነትን ሆኖ ሳለ፤ ጤነኛው ሰው ግን ስላለው ጤና አለማመስገኑ አይገርምም?
ካስተዋልነው አንዲት ቃል ህይወታችንን በርግጥም ትለውጣለች….. ለጠቢብ ሰው አንዲት ቃል ይበቃዋል ይባል የለ በማቴዎስ ወንጌል 25:29 “ ላለው ሁሉ ይሰጠዋል ይበዛለትማል…. ለሌለው ግን ያው ያለውም እንኳን ይወሰድበታል” የሚለው ቃል የሚያስረዳን ሁላችንም ለተሰጠን ማንኛውም መክሊት መጀመሪያ ምስጋና እናቅርብ ያኔ…ሌሎች በረከቶቻችንን፣ ይመጣሉ።
.
እግዚአብሔርንም ስለሰጠን ነገር ሁሉ ካመሰገንነው ባለን ላይ ሁሉ ለመጨመር አያመነታም።
ይቆየን!

share and join
@Ethio_Betecrstian
199 views05:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 09:29:00 እናታለም ኢትዮጵያ በታሪኳ ሕዝቦቿ ከሚያከብሯቸው በዓላት መካከል በጣም አሳፋሪ የሆነ በዓል ቢኖር ይህ ብሔር ብሔረሰቦች በዓል የሚሉት ነው።

በዚህ በዓል፦

➛ ከአንድነት ወደ መከፋፈል የመጣችበትን፣
➛ ከመቻቻል ወደ መገረፋፈጥ፣
➛ አንድ ከመሆን ወደ መገነጣጠል፣
➛ ከመደማመጥ ወደ አለመግባባት፣
➛ ከመከባበር ወደ መገፋፋት፣

የመጣችበትን ቀን ነው የምታከብር።

ሰው የአንድነት ቀን ያከበራል እንጅ የመለያየትን ቀን ያከብራል።

ለማንኛውም ብሔር ብሔረሰቦችየ እንኳን አደረሳችሁ ልላችሁ አሰብኩና ተውኩት!

@Ethio_Betecrstian
208 viewsedited  06:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 17:29:44
ምንጊዜም ቢሆን
፩) እግዚአብሔርን መፍራትን እናስቀድማለን።
፪) ፍቅረ ቢጽን እናስከትላለን
የሰው ልጅ ዋና ጌጦች ፍቅር፣ ትሕትና፣ እውነት ናቸው። ለሰው ልጅ ለተፈጥሮው የሚስማማ ትሕትና ነው። እውነትን መናገር ለእውነት መኖር ለእውነት መሞት ትእዛዛትን መፈጸም ፍቅረ እግዚአብሔር ነው። ሰውን እንደ ራስ መውደድ ደግሞ ፍቅረ ቢጽ ነው። ሰው እግዚአብሔርን ሲወድ እንደ ሕጉ ይሄዳል። ሰው ሰውን ሲወድ ደግሞ ለሌላውም እንደራሱ አድርጎ ያስባል ይጠነቀቃል። ለስነልቡናው ለአካሉ ለጠባዩ ይጠነቀቃል። መጻሕፍት ሰውን እንደ ራስህ ውደድ አክብረው አሉ እንጂ አሽቃብጥለት አምልከው ፍራው አላሉም። ማንኛውም ሰው በፈጣሪ ቸርነት የሚኖር ስለሆነ የሚፈራ አይደለም። የሚያሽቃብጡለትም አይደለም። መፍራትስ መገዛትስ ለፈጣሬ ሰማያት ወምድር ነው።
።
የፍቅር አምላክ ፍቅሩን ያድለን።
ፎቶ:-@ጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም ቤተክርስቲያን

share and join
@Ethio_Betecrstian
214 views14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ