ትናንት ደሴ ላይ በትክክል አገልግሎት ሲሰጡ ከነበሩ ባንኮች መካከል ዘምዘም፣ ሂጅራ፣ አዋሽና አባይ ባንኮች ይገኙበታል። ሌላውማ «ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ» እንዳላለን ሁሉ ተጫውቶብናል። በሰላሙ ቀን በየመንገዱ ላይ እያስቆሙ አካውንት ክፈቱ በማለት እንዳልተማጸኑን ሁላ ዛሬ ያስቀመጥነውን ስጡን ስንል ፊታቸውን አጠቆሩብን። እኔማ በተለይ 5 ኪሎና 6 ኪሎ አካባቢ መንገድ ላይ እያስቆሙ አካውንት ያስከፈቱኝን ባንኮች ዝርዝር ሁላ ረስቸዋለሁ። ብቻ ግን «ፎቶ የለኝም!» ስላቸው «ሐጂ፣ ሐጂ፣ ሸሁ፣ ሸሁ፤ ሌላ ቀን ታመጣለህ!» ብለው መቶ መቶ ብር መውሰዳቸውን ነው የማስታውሰው። አንዳንዶቹ አሁን ባለሁበት ሰፈር ጭራሽ ቅርንጫፍም የላቸው። ከሁሉም ጋር የሰጠሁትን መቶ ብር አውጥቼ አንድ ባንክ ላይ ባጠራቅመው ዘይት ይገዛልኝ ነበርኮ¡ ለማንኛውም ሰውን ስትፈልጉ ብቻ ሳይሆን ሰውም ሲፈልጋችሁ በቃላችሁ እየተገኛችሁ! 921 views"ųmį¥ę": , 07:59