Get Mystery Box with random crypto!

Ethio Smart market

የቴሌግራም ቻናል አርማ esayasauto — Ethio Smart market E
የቴሌግራም ቻናል አርማ esayasauto — Ethio Smart market
የሰርጥ አድራሻ: @esayasauto
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.14K
የሰርጥ መግለጫ

@Ethio_Smart_Market
╔╦╦═╦╔╦═╦═╦═╗
║ እንኳን ደህና መጡ ║
╚══╩═╩═╩╩╩╩═
»
Creater @esayasmart

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-11 09:27:30

264 viewsⒺSⒶYⒶS, 06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 09:25:37

261 viewsⒺSⒶYⒶS, 06:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 09:24:24

204 viewsⒺSⒶYⒶS, 06:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 09:22:45 https://www.youtube.com/channel/UCIEhxRPV303uN4CiwntU3iQ?sub_confirmation=1
187 viewsⒺSⒶYⒶS, 06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-21 15:51:16 Channel photo updated
12:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 13:31:49 በፌዴራል ፖሊስ የእውቅናና ምስጋና ምርሀ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ያስተላለፉት መልዕክት ዋና ዋና ነጥቦች

የእኛ አላማ ለእውነት የሚሰሩ፣ በእውቀት የሚመሩ ፣ በስነ ምግባር የዳበሩ፣
ሙያቸውን የሚያከብሩ ፣ ለህዝብ የሚኖሩ ፖሊሶችን ለኢትዮጵያ ማበርከት ነው፤

ሰዎች ሁሉ ፀጥ ረጭ ባለው ሌሊት በሰላም ተኝተዋል ምክንያቱም የማይተኙ ሰላም ጠባቂዎች ያለዕንቅልፍ ስለሚያድሩ ነው ይባላል ለዚህ ደግሞ ግንባር ቀደሙ የፌደራል ፖሊስ ነው፤

ሰላም እፈልጋለሁ ችግር የሚመጣ ከሆነ ግን በእኔ ዘመን እንዲመጣ እፈልጋለሁ፤ ምክንያቱም የእኔ ልጆች በሰላም እንዲኖሩ ስለምፈልግ የሚባለው አባባል በትክክል የሚሰራው ለኢትዮጵያ ፖሊስ ነው፤

የኢትዮጵያ ፖሊስ በጎችን ከተኩላዎች ለመጠበቅ 24 ሰአት የሚሰራ ሃይል ነው፤ ብዙ ተኩላዎች ሲጮሁ ይሰማል፤ የጩኸቱ ትርጉም በጎችን እንደፈለግነው እንብላ ተዉን ነው፤ ፖሊሶች ከተኩላዎች ምስጋና አይገኝምና ስራችሁን አጠናክራችሁ እንደትቀጥሉ እላለሁ ፤ ኢትዮጵያ አትፈርስም፤ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚፈልጉ ሃይሎች ይፈርሳሉ፤

ኢትዮጵያ ህልውናዋና ሉአላዊነቷ ለአደጋ በተጋለጠ ጊዜ ሁሉ ፖሊስ ግንባር ቀደም ተሰላፊ ነውና ክብር ይገባዋል፤ እናንተ የሰላም ዘቦች የብርሃን ጥቅም የሚታወቀው ጨለማ በሚሆበን ወቅት እንደ ሆነ ሁሉ የህግ አስከባሪዎች ሚና የሚታየውም ሰላምና ደህንነታችን አደጋ ሲወድቅ ነው፤

የሰላምን ዋጋ ብንገነዘብ ላፍታም ቢሆን ወደ ግጭት አናመራም ሰዎች ወደ መከራ ወደ ግጭት ሲገቡ የሰላም አስፈላጊነትን የሚገነዘቡ ቢሆንም የሰላም ዋጋ የረከሰ በመሆኑ ለእናንተ ሚናና ጥረት እምብዛም ክብር ያልሰጠን ቢሆንም ተኝተን የምናድረው ፣ አርሰን የምንበላው፣ ሀገራችን ለማበልፀግ የምንጥረው እናንተን ተማምነን ነው፤

በፖሊሶች የከሸፉ ወንጀሎችን ሳይሆን ከፖሊስ ዕይታ ያመለጡ ወንጀሎችን አግዝፎ የሚመለከት ባህል አለን፤ በየዘመናቱ፣ በየጊዜያቱና ቀናቱ ፖሊስ ለእኛ የማይነግረንን ብዙ ወንጆሎችን ያከሽፋል፤ ነገር ግን ያከሸፈውን የለፋበትንና መሰዋዕትነት የከፈለበትን ሳይሆን አልፎ አልፎ ከፒሊስ ዕይታ ያመለጠውን አብዝተን እንናገራለን፤

ፀጥታና ሰላማችንን ለማረጋጋጥ ሲዋደቁ ያላከበርናቸውን ፖሊሶች ወንጀል ሲፈፀምብን ጣታችን ልንቀስርባቸውና ልንወቅሳቸው አይገባም፤ ኢትዮጵያ በእጅጉ ለሚያገለግሏት ፖሊሶች በቂ ደሞዝ መክፈል ባትችልም እንኳን ማክበር መለማመድ ይኖርባታል፤

ኢትዮጵያ ከፍተኛ ዋጋ የከፈለችላቸው ያስተማረቻቸው ከምንም ወደ ገዘፈ ማንነት ያደረሰቻቸው ግለሰቦች የፖሊስን ግማሽ ዋጋ ቢከፍሉ ኢትዮጵያችን ምን ልትሆን እንደምትችል ላፍታ እንድታሰቡ እጠይቃለሁ።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
297 viewsⒺSⒶYⒶS, 10:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-05 13:30:50 Channel name was changed to «ESAYAS Auto️»
10:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-08 21:01:14 ESAYAS Auto️ pinned «ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ "የተፃፈ ደብዳቤ"ከአበበ ገላው!! ከሁሉም በማስቀደም አንኳን ለብርሃነ ልደቱ ከእነ መላ ቤተሰብዎ በሰላም አደረስዎ ለማለት እወዳለሁ። ይቺን አጠር ያለች ደብዳቤ እንድጽፍልዎ ያነሳሳኝ ዋና ጉዳይ የሚከተለው ነው። ኢትዮጵያ ከገባችበት ጥልቅ አገራዊ ቀውስ፣ ጦርነትና እልቂት ለማውጣት በአገራችን ብሄራዊ መግባባት ለማስፈን መንግስት እየወሰደ ያለው አንዳንድ እርምጃ ተገቢና…»
18:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-08 11:46:58 ለጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ
"የተፃፈ ደብዳቤ"ከአበበ ገላው!!

ከሁሉም በማስቀደም አንኳን ለብርሃነ ልደቱ ከእነ መላ ቤተሰብዎ በሰላም አደረስዎ ለማለት እወዳለሁ። ይቺን አጠር ያለች ደብዳቤ እንድጽፍልዎ ያነሳሳኝ ዋና ጉዳይ የሚከተለው ነው።

ኢትዮጵያ ከገባችበት ጥልቅ አገራዊ ቀውስ፣ ጦርነትና እልቂት ለማውጣት በአገራችን ብሄራዊ መግባባት ለማስፈን መንግስት እየወሰደ ያለው አንዳንድ እርምጃ ተገቢና ወቅታዊ በመሆኑ ሊበረታታ እንደሚገባ እምነቴ ነው።

በዚሁም መሰረት በእነ እስክንድር ነጋና በእነ ጃዋር መሃመድ የክስ መዝገብ ተከሰው በእስር ላይ ይገኙ የነበሩ እስረኞች እንዲፈቱ መደረጉ ተገቢ መሆኑ ብዙም አያከራክርም የሚል እምነት አለኝ።

ይሁንና በተያያዥ ተሰብሰብው፣ አቅደውና ከፍተኛ ዝግጅት አድርገው ጥቅምት 24 2013 በውድቅት ለሊት በሰሜን ዕዝ ላይ የተቀናጀ ጥቃት እንዲሰነዘር ትእዛዝ በመስጠት በበርካታ ሺ የሚቆጠሩ የአገር መከላከያ አባላት ላይ ግድያ፣ ዘግናኝ ግፍ፣ የአካልና የስነ ልቦና ጉዳት እንዲደርስባቸው የአንበሳውን ድርሻ የተጫወቱትን የአሸባሪው የህወሃት ከፍተኛ አመራር አባላት የሆኑትን እነ ስብሃት ነጋን መንግስት መፍታቱን ስሰማ የተሰማኝ ሃዘን እጅግ ጥልቅ ነው።

በእነዚህ ግልሰቦች ውሳኔ ምክንያት በህዝባችን ላይ ተዘርዝሮ የማያልቅ ግፍ ተፈጽሟል። ያም ሳያንስ በግለሰቦቹ ምክንያት አገራችን እስካሁን የጦርነት አረንቋ ውስጥ በመዳከር ላይ የምትገኝ ሲሆን ከመቶ ሺ በላይ ዜጎቻችን ህይወታቸውን እንዳጡ ይገመታል።

ሌሎች በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የአካልና የስነ ልቦና ጉዳት ሰለባ ከመሆናቸውም በላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ምስኪን ወገኖቻችን ከቀያቸው በመፈናቀል ለችግር፣ ርሃብና ቸነፈር ሰለባ እንዲሆኑ ምክንያት ሆነዋል።

ከዚህም በላይ በበርካታ ሺ የሚቆጠሩ እናቶች፣ ህጻናትና አዛውንቶች ሰይጣናዊ መንፈስ በተጠናወታቸው የህወሃት ታጣቂዎች እንዲደፈሩና ለአካላዊና ስነልቦናዊ ጉዳት ሰለባ እንዲሆኑ ምክንያት ሆነዋል። የግለሰቦቹ ተዘርዝሮ የማያልቅ ወንጀልና የሽብር ድርጊት ከማንም በላይ ለመንግስት ግልጽ ነው የሚል እምነት አለኝ።

በኢትዮጵያና ህዝቦቿ ላይ ተዘርዝሮ የማያልቅ ወንጀሎችን የፈጸሙና ወደፊትም ከመፈጸም ፈጽሞ የማይቦዝኑ ግለሰቦችን በዘፈቀደ መፍታት የህዝባችንን ጉዳት፣ ህመምና፣ ቁስል ፈጽሞ እያዩ እንዳላዩ ከማለፍ ወይንም ከማቅለል የማይተናነስ ሃላፊነት የጎደለው ድርጊት መሆኑን በሃቅ በመቀበል ውሳኔው በድጋሚ እንዲታይና ፍርድ ቤት ጉዳያቸውን አይቶ እንዲወስን እንዲደረግ በተጎጂ ወገኖቻችን ስም እጠይቃለሁ።

ከዚህም በተጨማሪ መንግስት በእርቅና ሰላም ስም የፍትህ ፈላጊውን ህዝብ ስሜትና ፍላጎቶች እንዲሁም የአገርን ደህንነት ከሚጎዳ ድርጊት መቆጠብ እንደሚገባው እንደ ዜጋ ለማስገንዘብ እወዳለሁ።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ሆይ!
መደመር በሚል ርእስ ባሰተሙት መጽሃፍ ገጽ 108 የሚከተለውን ጽፈው ነበር። "አንድ መሪ የተከታዮቹን ስሜት ካልተረዳና የስሜቶቹን ምክንያትና የሚያስከትሉትን ውጤት ካልመረመረ የስሜት ልቀቱ ላሽቋል ወይንም የስሜት ድቀት ውስጥ ገብቷል ማለት እንችላለን።

ህዝብና ተከታይ ሲከፋ ለምን እንደተከፋ መመርመር፣ የስሜቱን መጠንና አቅጣጫ ማጤን፣ እንዲሁም ስሜቱ ሊያስከትለው የሚችለውን አደጋ መገንዘብ አስፈላጊ ነው።...የህዝብን ብሶትና ንዴት በወቅቱና በተገቢ ሁኔታ ያልተረዳ መሪ ህዝብን እየገዛ እንጂ እየመራ አይደለም።"

እኔም እርስዎ በራስዎ ብዕር ከጻፉት ቁም ነገር የተለየ ሃሳብ ባይኖረኝም ቃልዎ ከተግባር ጋር መጣረሱን አስተውለው የመንግስትዎን ውስኔ መልሰው ይመርምሩ። ምንም እንኳን የኢትዮጵያ ህዝብ በቀልን ባይፈልግም ለዘመናት የተጠማውን ፍትህ ግን በፍርድ አደባባይ ማየትን እንደሚፈልግ አልጠራጠርም። ስለዚህም ይህ ውሳኔ የከፋ ጦስ ከማስከተሉ በፊት በጥሞና ተመርምሮ እንዲስተካከል ስል እንደ አንድ ፍትህ ፈላጊ ኢትዮጵያዊ መጠየቅ እወዳለሁ።

ይህ ሳይሆን ቢቀር ግን መንግስት ከፍተኛ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ኪሳራ ሊደርስብት እንደሚችል ፈጵሞ አያጠያይቅም። በመሆኑም ውሳኔውን መልሶ ማጤንና በአስቸኳይ መቀልበስ ተገቢ ነው የሚል እምነት አለኝ።

በተረፈ እንደ ታቀደው በጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ ከክፍፍል ይልቅ ብሄራዊ መግባባት እንዲሰፍን ምኞቴን እገልጻለሁ።

@ethio_mereja_news
1.0K viewsⒺSⒶYⒶS, 08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 18:44:59

632 viewsⒺSⒶYⒶS, 15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ