Get Mystery Box with random crypto!

Yihune Ephrem Kassahun

የቴሌግራም ቻናል አርማ ermiastokuma — Yihune Ephrem Kassahun Y
የቴሌግራም ቻናል አርማ ermiastokuma — Yihune Ephrem Kassahun
የሰርጥ አድራሻ: @ermiastokuma
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.81K
የሰርጥ መግለጫ

የተለያዩ መረጃዎችን ለመስጠትና በግል ለማናገር ለምትፈልጉ https://t.me/Ethiopiashallprevail ላይ በድምፅና በመልዕክት ታገኙኛላቹህ፡፡
በፌስቡክ facebook.com/ermitok ላይም አለሁ

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-28 06:45:35 “ይድረስ ለፈጣሪ ባለህበት”
ከባሪያህ ይሁኔ ኤፍሬም ካሳሁን

“እንደምን ከርመሀል እንዳልልህ የምታሳምም እንጅ የምትታመም አይደለህም፡፡ ደህና ነኝ እንዳልልህ ደህንነቴን ታውቃለህና አልደክምም፡፡ አንተ እኔ ምን እንደበላሁ፤ ምን እንዳማረኝ፤ መቼ ከሀገር አፍራሾች ሊስት ውስጥ እንደምገባ ታውቃለህ እኔ ግን አንተ ዘንድ ምን እየተፈጠረ እንዳለ ለማወቅ እጓጓለው ሠው ደካማ ነውና እንደጓጓው አለው እንጂ ያ ቀዩ መላኢክትህ መጥቶ መች ነገረኝ ብለህ፡፡


አምላክ ሆይ መንግስት ሰማያት እንዴት ነች “መንግስተ ሠማያት ቀርባለች እና ንስሀ ግቡ” እየተባለ እየተለፈፈ ባለበት ዘመን ስንቱ ከንስሃ በፊት በጅምላ ወደአፈር እንደገባ ታውቃለህ? እናስ ምነው መዘግየትህ ወይንስ እዛው የኢትዮጵያ እስር ቤቶች ሠብሠብ ብለን እንድንጠብቅህ ከጀልክ እንደሱ ካሠብክ መልካም በቅርቡ መምጣትህ አይቀርም!!!

ሲኦልስ እንዴት ናት ገሐነብ ውስጥ የቀድሞ የኢትዮጵያ መሪዎች ብዙ ሠው ገዳይ እኔ ነኝ የሚል ግብግብ ጀምረዋል አሉ ያናድዳል አንተም አናደኸኛል፡፡ መቼም አንተ ሁሉንም ነገር ተቆጣጣሪ ነህና በመናደዴ……. ባትቆጣኝ የምልህ ነገር አለኝ፡፡

ከዚህ እኔ ካለሁበት መንደር ያሉ ዲያቢሎስን ከሰማየ ሠማያት ወደምድር ስትወረውረው ምስራቅ አፍሪካ ነው ያረፈው እያሉ ያማሉ ኧረ እንዳውም ኢትዮጵያ ነው ይላሉ፡፡ እኔ ግን አልኩኝ ይሁና አንተ ሀያል ነህና ሣጥናኤል ቢያስቸግርህ ወደምድር ሠደደክው ወረወርከው እኛስ በሀገራችን ያሉ ሣጥናኤሎችን ወደየትኛው ህልቁ እንወርውራቸው፡፡ እኛ ጠዋት ማታ እንደድኩላ በስጋት መሸማቀቁ ሰልችቶናልና ይህን የተንኮል ማማሠያ የሚሰሩትን ሁሉ፤ ጥበባቸውን ድፍን አድርግባቸውና እኛም እንደልባችን ተንፈራጠን እንቀመጥ፡፡

አሁን እኮ መቼም ያለብን ስጋት እንዲህ አይምሰልህ፤ ሊያውስ መቼ አጣኸውና እነግርሃለው አንዱ አንድ ሲሠራ ሌላው ሌላ ይሠራል፡፡ ይኸውም እንዲህ መላ ቅጡ ጥፍት ባለው መንደር ውስጥ እየማልን ለአንተ መስገዱን ትተን፣ ለመሳሪያው ሠሪዎች መስገድ ጀምረናልና እንዳትቀርብህ ለራስህ ስትል አስብበት፡፡ የፖለቲከኞቹ ራዕይ ከዮሐንስ ራዕይ በላይ ገዝፎ ህዝብህ ፍርሃት ውስጥ ይገኛል፡፡ እኛን እንዲጠብቁ የመደብካቸው ጳጳሳት፣ ፓስተሮችና ሸሆችም እኛን መጠበቅ ትተው ለራሳቸው ወጠምሻ ወጠምሻ ጠባቂ ቀጥረውልሃል፡፡ እውነት እውነት እልሃለው መቼም እውነት መሆኑን ታውቃለህ ያው ስለለመደብኝ እውነት እውነት እልሃለው አንድያ ልጅህ ክርስቶስ እንኳን አሁን ላይ ቢመጣ ስለዚህ ህዝብ ነው የሞትኩት የሚል ይመስለኛል መቼም ይህንን ከሐጢያት እንዳትቆጥረው ይመስለኛል ነው ያልኩት፡፡

ለመሆኑ አንተ የምትመጣው መቼ ነው አንተ ትመጣ ወይስ እኔ ቸኩዬ ልምጣ መልሡን አንዱ ተላላኪህ ይዞልኝ ይምጣ አንተን አላስቸግርህም፡፡ ያለሐጢያት ለመገናኘት ያብቃን፤ ደህና ልሠንብት”

ባሪያህ ይሁኔ ኤፍሬም ካሳሁን
ከኮተቤ
806 viewsButies Bibies, 03:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-07 15:30:44 ትክክለኛ ኢትዮጵያዊ ባህሪይ ያለው መንግስት አግኝተናል!!!
መንግስታችን የኛን ባህሪይ ወርሶ እኛን መስሎ እያስተዳደረን መሆኑን ተገንዝባችሁት ይሆን? መንግስትም ልክ እንደህዝቡ ድህነትን ሳይሆን ደሃ መባልን የሚጠየፍ፤ የሚበላው ሳይኖረው 20 ሺህ ብር ስልክ ይዞ እንደሚቧዝን ህዝብ ለእይታ ብቻ የሚጨነቅ መንግስት፤ ችግረኛ ቤተሰቦቹን ከመርዳት ይልቅ ባለፀጋ ለመመስል ያገኛትን ብር ለገፅታ ግንባታ እንደሚጠቀም ምስኪን ኢትዮጵያዊ ፍጡር ስንት ረሃብተኛ ህዝብ ባለበት ሐገር ፏፏቴ ስር አፍሪካ መሪዎችን እራት በመጋበዝ ሐብታም መንግስት መስሎ መታየት የሚፈልግ ምስኪን፤ ውስጡ በመጠጥ ተቃጥሎ ጉበቱ ተጎድቶ ፊቱ ወዛም መስሎ እንደሚታይ ሰካራም አፋር ላይ ጭስ እያለ ሸገር ላይ ፈንዲሻ መስሎ የሚቀርብ መንግስት ኢትዮጵያን እየገዛ ነው፡፡
ከሰሞኑ እንኳን የአፍሪካ መሪዎች በየጎዳናው ያሉ ድሃዎችን አይተው እንዳይታዘቡን ድሃ ሀብታም ፊት እንዳይታይ ደብቀናል፤ ድህነትን ሳይሆን ደሃን ተጠይፈናል፡፡ ልክ እንደህዝባችን በድህነት መኖርን ሳይሆን ደሃ መባልን አጥብቆ የሚጠየፍ መንግስት ሾመናል፡፡ ይህ ሀገርና ህዝብ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም ላይ ለፈፀመው ክህደት ገና ስንት መስሎ መኖር የሚፈልግ፤ አእምሮውን ሳይሆን ውጫዊ ገፅታውን ማስተካከል የሚፈልግ መንግስት እንደሚመራት ፈጣሪ ይወቀው፡፡ እውነተኛው የኢትዮጵያ ድሃ ህዝብ መሪ ኮሎኔል መንግስቱ ይህ ሁሉ ሲሆን ቆሞ ያያል፤ አስመሳዩ እየተቀያየረ ኢትዮጵያን ይገዛል፤ ይበለን አዎ በደንብ ይበለን!!!! እዚህ ፅሁፍ ስር እየመጣህ መንጌ እንዲህ አደረገን እያልክ የምታላዝን በሙሉ አንተን የመሰለ መንግስት እየተፈራረቀ እየገዛህ ነውና እንኳን ደስ አለህ፡፡
3.1K viewsButies Bibies, 12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-11 11:45:56 ጤና ሚኒስትር በሚሊየን ገንዘብ በመክፈል የአፍሪካ ዋንጫን ስፖንሰር አድርጎ በነፃ ለተመልካቾች እያደረሰ ነው። ምን ያህል ኢትዮጵያውያን በህክምና እጦት ህይወታቸው እንደሚያልፍ ፈጣሪ ይወቀው።
3.5K viewsButies Bibies, 08:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-08 20:29:19 Live stream started
17:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-08 19:47:22 በእነስብሃት መፈታት ደስታቸውን የገለፁት መቀሌ ላይ ትግሬዎች መከለካያችንን እንደአውሬ የጨፈጨፉት እለት ጨፍረው እንደነበረ ማመን አለብን። በምንም ልትደሰት ትችላለህ ነገር ግን አንተ ተኝተህ እንድታድር ዳር ድንበር ሲጠብቅ የነበረን ሰራዊት አስተኝቶ እላዩ ላይ በሲኖ ትራክ የሄደበትን አራዊት እንኳን ተፈታ ብለህ መጨፈር እጅግ አረመኔነት ነው።
3.7K viewsButies Bibies, 16:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-03 09:49:14 ለአረንጓዴ ልማት፣ ለቤተ መፅሃፍትና ለተለያዩ ተግባራት እየተሰጠ ያለው ትኩረት ለኑሮ ውድነቱም ይሰጥ ብለህ ስትፅፍ ከዚህ ከዛም ይሰባሰቡና አንተ የአስተሳሰብ ችግር ስላለብህና የመቃወም ሱስ ይዞህ ነው ይሉሃል። እየበላህ አንብብ ሲባል ሰው እንዴት ይናደዳል?

በምግብ ራሱን ያልቻለ ማህበረሰብ ቢማርም ሆነ ቢያነብም የመለወጥ መጠኑ ዝቀተኛ እንደሆነ ነው ጥናቶች የሚያሳዩት፡፡ ድህነት አንድ ልጅ ለትምህርት ያለውን ዝግጁነት ይቀንሳል፤ የልጁን መረጃ የማሰባሰብ እና የማስታወስ ችሎታን፣ ትኩረትን፣ የማወቅ ጉጉትን እና ተነሳሽነትን ይቀንሳል፡፡

ነገሩን መንግስትን ከመደገፍና ከመቃወም ጋር ሳይሆን ከእውነታ ጋር እያያቹህ ሃሳብ ስጡበት፡፡ የኑሮ ውድነቱ ጣራ ነክቷል፤ ለሌሎች ዘርፎች የሚሰጠው ትኩረት ለኢኮኖሚውም ይሰጥ ማለት ችግሩ ምንድን ነው?
4.1K viewsButies Bibies, 06:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-01 20:17:26 የይመስለኛል ፖለቲካ

አንዳንድ የብሄር ፖለቲከኞች ደጋፊዎቻቸውን ለማሳመን የሚጠቀሟቸው ቃላቶች ያስቁኛል። ከእነዚህም መካከል አንደኛው የተወሰኑ ብሄሮች በማንነታቸው በስማቸው ጭምር እንዲሸማቀቁ ይደረግ ነበረ የሚለው ትልቁ ማሳመኛቸው ነው ሆኖም ይህ ደጋፊን ለማፍራት ሆን ተብሎ የተቀመረ ማሳመኛ ነው፤ ሰው በስም መጠሪያው እንዲሸማቀቅ ይደረግ የነበረው አሁንም የሚደረገው በአንድ ብሄር ላይ ብቻ ሣይሆን በኦሮሞውም፣ በደቡቡም በአማራውም ላይ ጭምር ነው። ጥሩ ምሳሌ ልንገራችሁ ድምፃዊ ኤልያስ ተባባል የተወለደው ጎንደር ነው አዲስ አበባ መጥቶ የሙዚቃ ካሴት ሊያሳትም አሳታሚዎችን ሲጠይቅ ትክክለኛ ስሙን ልዋጥህ ተባባልን ካልቀየረ ህዝቡ ካሴቱን እንደማይገዛው ተነግሮት ነው ከልዋጥህ ተባባል ወደኤልያስ ተባባል የቀየረው የማዲንጎ አፈወርቅም ስም ተቀይሮ እንደሆነ ሰምቻለሁ እርግጠኛ ባልሆንም ትክክለኛ ስሙ ተገኝ ነው የሚል ነገር ሰምቻለሁ፤ ተገኝ የሚለው ስም አሸማቆት ነው ማዲንጎ ያስባለው። በርካታ የአማራ ተወላጅ አዲስ አበባ ሲገባ ከድላርጋቸው ወደዳጊ ከእማዋይሽ ወደኤሚ ከፈለቀ ወደፊሊሞን ስሙን ይቀይራል። ይህንን የሚያደርጉት በስማቸው ምክንያት አዲስ አበባ ላይ የሚያጋጥማቸውን ተረብ በመፍራት ነው። በኦሮሞውም ላይ የሆነው ተመሳሳይ ነው በርካታ ኦሮሞዎች አዲስ አበባ ሲመጡ ስማቸውን ይቀይራሉ።

በነገራችን ላይ ሰውን በስም ማሸማቀቅ ኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ሀገር ያለ ነው ለምሳሌ የጀርመንን ብንመለከት Schartzmugel የሚለው ስም መጠሪያቸው የሆኑ ሴቶች በብዛት በስማቸው ይቀልድባቸዋል የእነርሱ ስም ዘመናዊ እንዳልሆነና እንዲቀይሩት ሲነገራቸው ልትሰሙ ትችላላችሁ በአንፃሩ Katrina በጣም ተወዳጅ የጀርመን ሴቶች ስም ነው። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰው በስሙ እንዲያፍር የሚደረገው ጎሣ እየተመረጠ አይደለም ከሁሉም ጎሳዎች ስም እየተመረጡ አዲስ አበባ ላይ ሰው ለመቀለድ ይሞክራል። ደሚቱ የሚለው የኦሮምኛ ስም ሲተረጐም ማሪቱ እንደማለት ነው ሆኖም በዚህ ሰአት ልጅህን ማሪቱም አልካት ደሚቱ ስሟን ሰምቶ የሚስቅ ሰው አታጣም ይህ የሰው ልጅ ለስም ካለው ግምት የሚነሳ ነው እንጂ አንዱን ጎሣ በመናቅ ሌላውን ለማሞገስ ተብሎ የሚደረግ ነገር አይደለም አልነበረምም።

ኢትዮጵያውያን ከሚለያዪን ነገሮች ይልቅ የምንመሳሰልባቸው ነገሮች እልፍ አእላፍ ናቸው፤ ሊለያዩን የሚሯሯጡትን እያስወገደን አንድነታችንን ማጠናከሩ ለሁላችንም መልካም ነው።
3.6K viewsButies Bibies, 17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-25 16:28:26 ተስፋየ ገብረአብ እኮ ......

ተስፋዬ ገብረአብ ደርግ ሊወድቅ አካባቢ ፕሬስ መምሪያ ውስጥ ሲሰራ ቅልጥ ያለ የኢሠፓ ደጋፊ ነበረ፤ ጦርነት ለመዘገብ በረሃ ወርዶ በወያኔ ሲማረክ ቀንደኛ የህወሃት አባል ሆነ፤ ሕወሃት ስልጣን ሲይዝ የህወሃት አመራሮችን ለማስደሰት ሲል በአማራውና በኦሮሞው መካከል ግጭት ለመፍጠር ልቦለድ ፅፎ ታሪክ ፃፍኩ አለን፤ ከህወሃት ጋር ያለው ፍቅር ጋብ ሲል በኬንያ አድርጎ ደቡብ አፍሪካ ከገባ በኋላ ወደኤርትራ በመሄድ የሻእቢያ አፈቀላጤ ሆነ፤ ሆላንድ ሲገባ ደግሞ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ መፅሀፉ ላይ አስተያየት እንዲጽፉ በመለመን የግንቦት ሰባት ደጋፊዎች ልብ ውስጥ ለመግባት ሞከረ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ስለመፅሃፉ አስተያየት ቢፅፉለትም ያሰበው ነገር አልሳካለት ሲል ወደኦነግ በመቅረብ ኦሮሞ ነኝ ሲል ሆላንድ ላይ በተካሄደው የኦሮሞ ኮሚኒቲ ኮንፍረንስ ላይ ተናግሮ ኦሮሞ መስሎ ኦነጎች ማንበብ የሚፈልጉትን እየፃፈ መጠቀም ፈለገ።
ተስፋዬ ገብረአብ የተሻለ ጥቅም አገኝበታለሁ ብሎ በሚያስብበት ሁሉ የሚገኝ ግለሰብ ነው፤ ተስፋዬ ገብረአብ ከስነፅሁፍ ችሎታው ውጭ ምንም አይነት ሰውኛ ስብእና የሌለው ግለሰብ ነው።

ተስፋዬ ገብረአብን ከስነፅሁፍ ችሎታው ውጭ የማደንቅለት ነገር ቢኖር የኢትዮጵያ ፖለቲከኞችን ድክመት በደንብ ያውቃል በድክመታቸውም እንደፈለገው ይጫወትባቸዋል። ጎበዝ ፀሃፊ እንደነበረ ግን ሁሉም ያምናል!

ነፍስ ይማር!
3.0K viewsButies Bibies, 13:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-22 06:22:27 ስለድርድር አብዝቶ እየተወራ ነው፤ ግልፅ ሊሆንልኝና ማንም ሊያስረዳኝ ያልቻሉ ጉዳዮች አለ።

1, ብልፅግና ማንን ወክሎ ነው የሚደራደረው? የሞተው ድሃው ህዝብ ነው። ሚስቱና እህቱ የተደፈረችበት ሲቪሉ ሆኖ ሳለ ድርድርም ካስፈለገ ሀሳቡ በጦርነቱ ከተጎዱ ንፁሃን መምጣት እያለበት ብልፅግና ስለድርድር የሚያወራው ማንን ወክሎ ነው? እውነት ህዝቡ ላይ ስለደረሰው ግፍ ባለስልጣኖቻችን በትክክል ያውቃሉ?

2, ይሄ እኮ የብልፅግና ጉዳይ አይደለም፤ ጦርነቱ የኢትዮጵያና የትግሬ ወራሪ ቡድን እንጂ የብልፅግና እና የህወሃት አልነበረም። ህዝብ የሞተው ሀገር ለማዳን እንጂ የብልፅግና ባለስልጣናትን ስልጣን ለማራዘም አይደለም።

በመጨረሻም ድርድር ከተባለ በግሌ ልደግፈው የምችለው ድርድር ወልቃይትና ራያ ወደታሪካዊ ድንበራቸው ተጠቃለው የአማራ ንብረት ሲሆኑ፤ የህወሃት መሪዎች ለፈፀሙት ግፍ በህግ ለመጠየቅ ፍቃደኛ ሆነው እጃቸውን ሲሰጡና የትግሬ ወራሪ ቡድን ከአማራና ከአፋር ለዘረፋት ንብረት ተገቢውን ካሳ ሲከፍል ነው። ይህ ሳይፈፀም ቀርቶ ብልፅግና ወደድርድር ከገባ ምንም የሚያስፈራን ነገር ስለሌለ ዳግመኛ ትግላችንን እንጀምራለን። ድሮም ቢሆን ህወሃትን የታገልነው እኛ እንጂ ብልፅግና አይደለም።
3.1K viewsButies Bibies, 03:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-21 08:46:19
"ለሰራዊታችን ውሃና ምግብ አቅራቢ ነበርን፤ ዛሬ ግን ተዘርፈን ቤታችን ባዶ ሆኖ በዚህ የድል ቀን ለሰራዊታችን ውኃ እንኳን ማቅረብ አልቻልንም።" ይቅር በሉን
2.7K viewsButies Bibies, 05:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ