Get Mystery Box with random crypto!

ኤጲፋንዮስ🌹

የቴሌግራም ቻናል አርማ epiphanios1 — ኤጲፋንዮስ🌹
የቴሌግራም ቻናል አርማ epiphanios1 — ኤጲፋንዮስ🌹
የሰርጥ አድራሻ: @epiphanios1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 281

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-01-07 03:15:36 በላሊበላ ያሉ ሊቃውንት እንዲህ ብለው እግዚአብሔርን ይለምናሉ
"እቀቡኒ ለበግዕክሙ እምአፈ አናብስት ወተኩላ
ነአኩቶ ለአብ ይምራሐ ገብረ ማርያም ወላሊበላ"
ደፍሮ ከሚያጠቃ አንበሳ እና ተደብቆ ከሚነጥቅ ተኩላ ስለ ነገስታቱ ቃልኪዳን ብለህ ጠብቀን እያሉ ይማፀናሉ፤እኛንም ስለነሱ ብለህ ማረን ጠብቀን ለዘለዓለሙ አሜን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር


እንኳን ለብርሐነ ልደቱ በሰላም እና በጤና አደረሳቹ

ከዲያቆን ኢዮብ ጌታቸው
(
@Eyob12213)
ጌና(ገና) በዓል
ከባህር ዳር
Groups
@Epiphanios2
Channel
@Epiphanios1
Tik tok
@epiphany21_1
Facebook
Eyob getachew
29/04/2015 ዓ.ም
594 viewsEyob Getachew, 00:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 03:15:36 ከራድዮን እና ህመምተኛው በአንድ ላይ ተፈውሰው እስኪድኑ ድረስ ይበራል።ምሳሌነቱ፦"የዚህ ዓለም ግዢ ይመጣልና በእኔ ላይ ምንም ምን ዕዳ አያገኝም"ብሎ እርሱ እራሱ እደተናገረ።
ዮሐ 14፥30
"ምርኮን ማረከኽ ወደ ሰማይ ወጣኽ"።
መዝ 67:12
የጌታችን በዓለ ጌና በታኅሣሥ ወር ይከበራል።
ይህም ሊታወቅ ታኅሣሥ የሚለው ቃል "ኀሢሥ ኀሢሦት" ከሚለው የግእዝ ንኡስ አንቀጽ የወጣ ሲኾን ማሰስ፣መሻት፣መመርመር ማለት ነው።ወርኀ ታኅሣሥ ማለት የፍለጋ ወራት ማለት ነው።ይህም ጌታችን ሲወለድ ሦስቱ ነገስታት "አይቴ ሀሎ ዘተወልደ ንጉሠ አይሁድ እስመ ርኢነ ኮከበ ዚአሁ በምሥራቅ ወመጻእነ ከመ ንስግድ ሎቱ"(ኮከቡን በምስራቅ አይተን እንሰግድለት ዘንድ መተናልና የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው።)እያሉ መጥተው አግኝተውት ወርቅ፣ዕጣንና ከርቤ ገብረውለታልና፤ለወሩ ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል።

ጌና እና ገና
አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በሰዋሰው ወግስ መጽሃፋቸው ላይ "ጌና :-ገና የልደት ዋዜማ ድራር።ገሃድ ወይም ልደት፤በዓለ ልደት።"ብለው ይገልፁታል።
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመጽሃፈ ብርሐን መጽሃፋቸው ላይ የጌና ንባብ ብለው በመቀጠል፤ የገና ንባብ ብለው ጽፈው ልዩነቱን ገልፀዋል።
ልደት
በእስራኤል ዘንድ ህፃን ሲወለድ የሚፈጸም ስርዓት ነው።
ዘሌ. 12
"ክርስቶስ ሕግን ለመፈጸም ስለተወለደ የሕግ ስርዓት ተፈጸመለት።"
ሉቃ. 2፥21-24
"1፤ በዚያም ወራት ዓለሙ ሁሉ እንዲጻፍ ከአውግስጦስ ቄሣር ትእዛዝ ወጣች።2፤ ቄሬኔዎስ በሶርያ አገር ገዥ በነበረ ጊዜ ይህ የመጀመሪያ ጽሕፈት ሆነ።3፤ ሁሉም እያንዳንዱ ይጻፍ ዘንድ ወደ ከተማው ሄደ።4-5፤ ዮሴፍም ደግሞ ከዳዊት ቤትና ወገን ስለ ነበረ ከገሊላ ከናዝሬት ከተማ ተነሥቶ ቤተ ልሔም ወደምትባል ወደ ዳዊት ከተማ ወደ ይሁዳ፥ ፀንሳ ከነበረች ከእጮኛው ከማርያም ጋር ይጻፍ ዘንድ ወጣ።"
ሐተታ
"አምላክ አዳምን በህይወት መጽሐፍ ውስጥ ሊጽፈው በፈለገ ጊዜ ህዝብ በህዝብ ቆጠራ ሊመዘገብ ትእዛዝ ወጣ።ትእዛዛቱም አንድ ላይ ተጣመሩ።አንዱ ከላይ ከጌታ አንዱ ከታች ከቄሳር።ቄሳር ሰብአዊ ቆጠራ ይመዘግባል ወልደ እግዚአብሔር ግን ሰዎችን በህይወት መጽሐፍ ያትማል።"አለ።
እነዚህ ቆጠራዎች እግዚአብሔር ባወቀ የሆኑ ናቸው።
"3፤ ሁሉም እያንዳንዱ ይጻፍ ዘንድ ወደ ከተማው ሄደ።"

ሐተታ
አዳም ወደገዛ ከተማው(ወደ ገነት) ሊመለስ እንደተቃረበ ያጠይቃል።
"4-5፤ ዮሴፍም ደግሞ ከዳዊት ቤትና ወገን ስለ ነበረ ከገሊላ ከናዝሬት ከተማ ተነሥቶ ቤተ ልሔም ወደምትባል ወደ ዳዊት ከተማ ወደ ይሁዳ፤"

ሐተታ
ቤተልሔም ማለት የእንጀራ ቤት ማለት ነው።የህይወት እንጀራ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ የዳዊት አምላክ እና ፈጣሪ ሲሆን በቤተልሔም ሊወለድ እንደሆነ ያናገረውን ትንቢት እንደ ደረሰ እንደ ተፈጸመ የጠይቃል።
"ኢየሱስም በይሁዳ ቤተልሔም በንጉሥ ሄሮድስ ዘመን በተወለደ ጊዜ ሰብአ ሰገል የተወለደው የአይሁድ ንጉስ ወዴት ነወ? ኮከብን በምስራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናል እያሉ ከምስራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ።"

ማቴ 2፥1
የማቴዎስን ትርጓሜ ሐተታ ስንመለከት እንዲህ ይገልጸዋል
:-ለምን ቤተልሔምን መጥቀስ አስፈለገ?
ትንቢቱን ለመፈጸም
"አንቺ ቤተልሔም ኤፍራታ ሆይ የይሁዳ ምድር ከይሁዳ ገዢዎች ከቶ አታንሺም ህዝቤ እስራኤልን የሚጠብቅ መስፍን ካንቺ ይወጣል" የሚል ነው።
ምሳሌው ለማመልከት
ታሪኩ በት.ሚክ 5፥2 ይገኛል።ካሌብ ከኢያሱ ላይ ኬብሮንን ጠይቆት ይወስዳል።እሱን እጅ አድርጎ አዙባ የምትባል ሴት አገባ።እሷም ከጠላት ወገን ስለነበረች የኬብሮንን መሬት በእሷ ስም አልሰየመውም።በመቀጠል ከብታ የምትባል አገባ።ኬብሮንን ከብታ በምትባል ሚስቱ ስም አረገው።እንደገና ኤፍራታን ሲያገባ በኤፍራታ ኤፍራታ ተባለ።ካሌብ ወንድ ልጅ ከእሷ ወለደ።ያጊዜ በሀብት ላይ ሀብት ሲያገኝ የልጁን ስም ልሔም አለው።ልሔም ማለት ህብስት ማለት ነው።በመጨረሻም በልሔም ቤተ-ልሔም ተባለ።
ከብታ ማለት ቤተ-ስብሐት ማለት ነው።
ቤት:- እመቤታችን
ስብሐት:-ጌታችን

ኤፍራታ ማለት ጸዋሪተ ፍሬ (ፍሬን የምትሸከም) ማለት ነው።
ጸዋሪት:-እመቤታችን
ፍሬ:-ጌታችን
ቤተ-ልሔም ማለት ቤተ-ኅብስት ማለት ነው።
ቤት:-እመቤታችን
ልሔም:-ጌታችን

ለምን ንጉሥ ሄሮድስን መጥቀስ አስፈለገ?
በጌታ መወለድ ምክንያት የተደናገጠው ሄሮድስ 14 እልፍ ህፃናትን ሲገል ስለሚጠቅሰው።
በእስራኤል ልማድ ዘመን ሲቆጠር በንጉሥ ነውና አነሳው።
ሰማያዊ ንጉሥ መወለዱን ለማሳየት ምድራዊውን ሄሮድስን ጠቀሰ።

የጌታችን በበረት መወለድ
ወንጌላዊው ሉቃስ የጌታን በበረት መወለድ እንዲህ ገልጾታል፦
" የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥ በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው በግርግም አስተኛችው።"

ሉቃ 2:7
ትንቢቱ ሊፈጸም በበረት ተወለደ
" በሬ የገዢውን አህያም የጌታውን ጋጣ አወቀ፤ እስራኤል ግን አላወቀም፥ ሕዝቤም አላስተዋለም። "
ት.ኢሳ 1:3
"በማዕከለ ክልኤ እንስሳ ርኢኩከ"
(በሁለት እንስሶች መካከል አየሁክ)
ይህ ማለት በበረት ውስጥ በአህያ እና በላም መካከል አየሁ ማለት ነው።

"ወጠብለለቶ በአጽርቅት"
ሉቃ 2፥7
ሐተታ
በጨርቅ ጠቀለለችው ብታጣ አንድም ምትሐት እንዳይደለ ለማጠየቅ።አንድም ዮሴፍ ኒቆዲሞስ በድርብ በፍታ እንዲህ ይገንዙሃል ስትል አንድም ካህናት ዕለት ዕለት። ሥጋህን ይጠቀልሉታል ስትልህ።
ሰብአ ሰገልም ከሩቅ ሀገር በኮከብ ተመርተው ወደ ኢየሩሳሌም መጡ።ኮከብ እየመራቸው ስንል ኮከብ መሣይ ብርሐን ስለነበረው ነው።ነገር ግን እነሱም እደተመለከቱት ቅድስት ማርያም ልጇን ኢየሱስን ታቅፋ ነበር የታያቸው።እሱ እየመራቸው ቤተልሔ ደረሱ።ሦስት ነገስታት ነበሩ እያንዳዳቸው 10 ሺህ ወታደሮች ነበሯቸው።ወደ ኢየሩሳሌም ሲመጡ ህዝቡም ደነገጠ፤ሄሮድስም ተደናገጠ እናም ሊቃውንቱ አስጠርቶ ነገሩን ተረዳ።ሰብአ ሰገልም ሄሮድስን ጋር ሄደው ጠየቁት መልሱን ተቀብለው ወደ ቤተልሔም ደረሱ።
"ጌታ ኢየሱስ በዚያች ዕለት ወደ ቤተልሔም መጡ፤ሰብአ ሰገልም አገኙአቸው፤የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ያለ ናዝሬት በሌላ ቦታ አላደገምና፤ ከተወለደም እድሜው ሁለት ዓመት ሆኖት ነበርና"

መፅሃፈ ስንክሳር ዘወርኃ ታኅሣሥ 29
ለጌታችንም ሰግደው ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤ ገበሩለት።
ወርቅለመንግስቱ፤የሃይማኖት ምሣሌ ነው።
ዕጣንለክህነቱ፤የተስፋ ምሣሌ ነው።
ከርቤለሞቱ፣ለህማሙ፤የአንድነት ምሣሌ ነው።
ኢየሱስ በቤተልሔም ሲወለድ "ዮም ተወልደ መድኀኔ ዓለም ቤዛ ኵሉ ዓለም ዮም ተወልደ ከሣቴ ብርሐን" እያለች ሚዳቋ መስክራለች።
1.4K viewsEyob Getachew, 00:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 03:15:36
29/04/2015ዓ.ም


[ ስለ ልደት በዓል ምስጢር እና ትንታኔ በዲያቆን ኢዮብ ጌታቸው። ]


እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሐነ ልደቱ በሰላም እና በጤና አደረሳቹ።

"ዮም ተወልደ መድኀኔ ዓለም
ዮም ተወልደ ከሣቴ ብርሃን"
(የዓለም መድኃኒት ዛሬ ተወለደ
ብርሃንን የሚገልጥ ዛሬ ተወለደ)

ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ

ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ስምረቱ ለሰብዕ ብለን የስብከት የትምህርት የምስጋናን ነገር እናገራለሁ።
ቅዱስ ያሬድ በማኅሌቱ
"ለዘተወልደ እም ቅድስት ድንግል ምንተ ንብሎ ናስተማስሎ ለመድኀኒነ ዓርዌ ገዳምኑ አንበሳ ወሚመ ከራድዮን"

(ከእመቤታችን የተወለደውን ምን ብለን እንጠራዋለን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በምን እንመስለዋለን በዱር አውሬ አንበሳን ነው ወይስ ከራድዮን በሚባል ወፍ ነው።) አለ።
አንበሳን እና ከራድዮንን ለምን ማንሳት አስፈለገ?
አንበሳ፦ይህም የአንበሳን ዐዋቂነቱን ያስረዳል፤በዋሻው ውስጥ በተኛ ጊዜ ዐይኖቹን እና ቅድቦቹን ገልጦ ያልተኛ ይመስላል።ይህም ምሳሌ በመስቀል ላይ በሞተ ጊዜ ነፍሳትን የሸነገለ ሰይጣንን የተጠበበበት በኾነ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ይፈጸማል።ጠቢብ ሰሎሞን "እኔ የተኛኁ ነኝ፤ልቤ ግን ነቅታለች"ብሎ ገልፆታል።
ከራድዮን፦ሁለመናው ነጭ ፀጉር የሆነ ወፍ ነው።በነገስታት ቤት ውስጥ ነው የሚገኘው።አንድ ሰው በጽኑ ህመም ከታመመ እና ለሞት የሚያደርሰው ከሆነ ከራድዮን ወደ ህመምተኛው ሄዶ ያየዋል የህመምኛውን በሽታ ተቀብሎ ወደ አየር ይበራል።የፀሐይ ግለት እስኪያቃጥለው፤
483 viewsEyob Getachew, 00:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 23:24:15 @epiphanios2
37 viewsEyob Getachew, 20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 23:24:15 @epiphanios2
35 viewsEyob Getachew, 20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 23:24:15 @epiphanios2
35 viewsEyob Getachew, 20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 23:24:15 @epiphanios2
34 viewsEyob Getachew, 20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 23:24:15 @epiphanios2
34 viewsEyob Getachew, 20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 23:24:14 @epiphanios2
31 viewsEyob Getachew, 20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-05 23:24:14 @epiphanios2
30 viewsEyob Getachew, 20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ