Get Mystery Box with random crypto!

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሸገር ከተማ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲዋቀርና ብፁዕ አቡነ ሳዊሮ | EOTC TV

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሸገር ከተማ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲዋቀርና ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ሊቀ ጳጳስ ተመድበው እንዲያደራጁ ውሳኔ ማሳለፉ ተገለጸ።

ኢኦተቤ ቴቪ ሰኔ ፳፱/፳፻፲፭ ዓ/ም

በኦሮምያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በአዲስ አደረጃጀት እየተዋቀረ የሚገኘው የሸገር ከተማ በስፋቱና በውስጡ ከሚይዛቸው አብያተ ክርስቲያናት አንጻር በሀገረ ስብከት ደረጃ ሊቋቋም የሚገባው ከመሆኑም በተጨማሪ በማስተር ፕላኑ ምክንያት የአብያተ ክርስቲያናቱ የይዞታ ቦታዎችን በተመለከተ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ተጠሪ ሊቀጳጳስ የሚያስፈልገው መሆኑን ጉባዔው በእጅጉ መረዳቱ ተገልጿል፡፡

በመሆኑም የሸገር ከተማ ጉዳይ ወቅታዊና ጊዜ የማይሰጠው ተግባር ስለሆነ በሀገረ ስብከት ደረጃ እንዲቋቋምና ሀገረ ስብከቱንም
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣ በምሥራቅ አፍሪካ የኬንያ፣ የኡጋንዳ፣ የሩዋንዳና ታንዛኒያ አህጉረ ስብከት እና የምስካዬ ኀዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ሊቀጳጳስ ተመድበው እንዲሚያደራጁትም ታውቋል፡፡

በአዲስ መልኩ በሚዋቀረው የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የበጀትና የሠራተኞችን ጉዳይ በተመለከተ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል ተጠንቶ ለጥቅምት 2016 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንዲቀርብ ይደረግ በማለት ምልዓተ ጉባኤው ውሳኔ ማሳለፉን ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡
EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++



"የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ"
የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት
የዲጂታል ሚዲያ ገጾች
ለመረጃ +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2



➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY=