Get Mystery Box with random crypto!

እናት ፓርቲ - Enat Party

የቴሌግራም ቻናል አርማ enat_party — እናት ፓርቲ - Enat Party
የቴሌግራም ቻናል አርማ enat_party — እናት ፓርቲ - Enat Party
የሰርጥ አድራሻ: @enat_party
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.72K
የሰርጥ መግለጫ

እንኳን ወደ እናት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ገጽ በሰላም መጡ።
ስለተቀላቀሉን እናመሰግናለን።

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-26 12:09:54 #አዲስ_አበባ_የሁሉምና_ለሁሉም_እንጂ_የጥቂት_ግለሰቦች_ፍላጎት_ማስፈፀሚያ_አይደለችም!
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት፣ መኢአድ እና ኢሕአፓ የተሰጠ መግለጫ
በሕገ መንግስቱ ላይ የተቀመጠን “ልዩ ጥቅም” እጅግ በመለጠጥ ከተማዋን የ”መጠቅለል” ወይም “ጥቅም አልባ” ማድረግ በሚመስል አካሄድ እየተሠራ ያለው ደባ ከሌሎች ዘርፈ ብዙ ችግሮች ጋር ተጋግዞ ለከፋ አደጋ እያጋለጣት ነው። ጊዜያዊ ስልጣንን መከታ አድርገው መሬት እየሸጡ እየለወጡ መኪና ሲቀያይሩ፣ ጠጅና ጮማ ሲያወራርዱ ያልጠሩትን ሕዝብ ክፉ ሥራቸው ሲጋለጥ መሸጎጫ በማድረግ ከጮማው አግልለውት ከሞታቸው ይጠሩታል፡፡
የከተማዋን ነዋሪዎች አልፎም መላው ኢትዮጵያውያንን የሚያውክ አካሄድ በገዢው መንግስት በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት እየተፈጸመ ነው። ውሳኔው የቦታ ጉዳይ ብቻ ተደርጎ የሚታይበት መንገድም ፈጽሞ ስሕተት ሲሆን ከቦታ በዘለለ በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ የከተማይቱን ነዋሪዎች መብት የሚጥስ ድርጊት ነው።
በአዲስ አበባ ከተማ እና በኦሮሚያ ክልል መካከል ይካሔዳል የተባለው ሂደቱን ያልጠበቀ፣ ሕግን ያልተከተለ የወሰን ማካለል በአስቸኳይ እንዲቆም እናሳስባለን፡፡
“ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ!"
እናት ፓርቲ፣ መኢአድ እና ኢሕአፓ
ነሐሴ 20 ቀን 2014 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
https://www.facebook.com/105146947885320/posts/pfbid026gbisW2D7Qfe2Ef89cku4CRnDHcL13MJa3P4MB59js533cwfMrLmhpqd2EBBJjtAl/?app=fbl
340 views09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 16:34:46 #ዜና
#እናት_ፓርቲ_ለአማራ_ብሔራዊ_ክልላዊ_መንግሥት_በክልሉ_ስላለው_ፍትሕን_በሚመለከት_ጉዳይ_ደብዳቤ_ጻፈ።
እናት ፓርቲ ደብዳቤውን የጻፈው ለክልሉ ፕሬዝዳንት ክቡር ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ሲሆን የደብዳቤው ይዘት በክልሉ ስላለው የፍትሕ አሰጣጥ ጉዳይ ነው።

ፓርቲው ማንም ሰው ከሀገር ሕልውና እና ከሕግ በላይ አይደለም ብሎ በጽኑ እንደሚያምን እንዲሁም ማንም ሰው ተጠርጥሮ ሊያዝ እንደሚችል ነገር ግን በእልህና ማን አለብኝነት የፍትሕ ሥርዓቱ በተሸረሸረ ቍጥር ዜጎች በፍትህ ሥርዓቱ ላይ ያላቸውን አመኔታ ያሳጣል ብሏል። ስለሆነም ኹሉም ነገር በሕግ፣ አባቶቻችን ባቆዩልን የሞራል ከፍታ እና ማኅበረሰባዊ እሴት መምራት አኹን በሳባታሚት ማረሚያ ቤት ያሉትን ወንድሞቻችንን ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የክልሉን ሕዝብ ወዲህም ሀገራችንን የሚጠቅም ተግባር በመሆኑ ክቡር ፕሬዝዳንቱ ከፍትሕ ጉያ ወጥቶ ፖለቲካዊ ጥላ ውስጥ በገባው በእነዚህ ወንድሞቻችን ጉዳይ መንግስታቸው ጣልቃ ገብቶና የተፈቀደላቸው የዋስ መብት እውን ሆኖ ከሚወዷቸው ቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲቀላቀሉ፣ ፍትሕም ሳትሸራረፍ መተግበሯን እንዲያረጋግጡ ሲል ጠይቋል።
እናት ፓርቲ
ነሐሴ 5 ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
665 views13:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 16:57:24 #የክልል_እንሁን_ጥያቄዎች_ዘላቂ_ሰላምን_በሚያመጣ_መልኩ_ሊፈቱ_ይገባል!
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

ሀገራችን ኢትዮጵያ ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ የተዋቀረችበት የ”ክልል” አደረጃጀት ኢትዮጵያውያን ልጆቿ ለሦስት ሺህ ዓመታት አብረው የኖሩበትን እንዲሁም በሰላምና በመቻቻል ተጋግዘው የመኖር እሴታቸውን ያጠፋና ሀገራችንን ለከፋ ችግር የዳረገ አወቃቀር መሆኑን እናት ፓርቲ በጽኑ ያምናል፡፡
ኢትዮጵያውያን ለበርካታ ዓመታት የታገሉለት ጥያቄ ኹሉንም ዜጋ በእኩልነት የሚያስተናግድና በሚናገሩት ቋንቋ፣ በሚከተሉት ሃይማኖት እና የፖለቲካ ዝንባሌ የማያገልል፣ ሀገር ያላትን በረከቶች በእኩልነትና ግልጽነት የሚያቋድስ፣ አንድነትን፣ እድገትንና ዘላቂ ሰላምን ለድርድር የማያቀርብ ሥርዓት እንዲዘረጋ እንጂ በየጊዜው ወደ እርስ በእርስ ግጭት የሚከትና ለአላስፈላጊ የሕይወት መሥዋዕትነትና ንብረት ውድመት የሚዳርግ ቀውስ ውስጥ ለመግባት አልነበረም።
ፈጣሪ ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ
እናት ፓርቲ
ነሐሴ ፬ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

https://www.facebook.com/105146947885320/posts/pfbid028DGZZoaL7bwk6mrT1i2zmAFwWDuZWARf8BbTwPZKU3JMeaK1U33NP1gkBXEWym5Jl/
633 views13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 10:10:39 #ዜና
ከአማራ ክልል ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ መንገዶች ላይ የሚደርሰው እንግልት ከጊዜ ወደጊዜ እየከፋ መሆኑ ተገለጸ።
ይህ እንቅስቃሴ በወለጋ ላይ ማንነትን መሰረት አድርጎ የሚፈጸመው ጭፍጨፋ መልኩን ቀይሮ የመምጣቱ ማሳያ ነው።
ፈጣሪ ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ
እናት ፓርቲ
ሐምሌ ፳፰ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
786 views07:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 14:36:20 #አልሸባብ_በጀግኖቹ_ተመትቷል_ይበልጥ_ግን_ትኩረት_ይሻል!
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
በአንጻራዊነት ሰላም በሰፈነበት እና ለሌሎች ክልሎች ምሳሌ መሆን በሚችለው የሦማሌ ክልል ላይ የአልሸባብ የሽብር ቡድን ሀገርን ለማተራመስ ከቀናት በፊት በአፍዴር ዞን መግባቱን ተከትሎ በክልሉ ልዩ ኃይል ነበልባል ክንድ ተደቁሶ ሕልሙ ሳይሳካ ሀሳቡም ሳይሞላ ለእኩይ ዓላማው መጠቀሚያ የያዛቸው ተሽከርካሪዎች ተቃጥለዋል፣ ትጥቁም፣ ስንቁም ተማርኳል።
ፈጣሪ ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ
እናት ፓርቲ
ሐምሌ ፳፮ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
https://www.facebook.com/105146947885320/posts/pfbid0NUy9XTaHRdHknGLcPMrLsknaFdbV9HTKRYLMePdo8gXcHabjK3HEfaV7GzcZJnw2l/
254 views11:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 10:57:10 #ሊበሏት_ያሰቧትን_አሞራ_ጅግራ_ናት_ይሏታል!
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
ከዚህ በፊት ለሃያ ሰባት ዓመታት ተቋሟን ለሁለት በመክፈል ቤተ ክርስቲያኒቱን የማዳከም ተንኮል ሸራቢዎች ያለፈው ስህተት ሳይጸጽታቸው “ጊዜው የእኛ ነው” ባዮች መሰል ድርጊት ለመፈጸም የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ታሪክን መልሶ ለመድገም የሚደረግ ደባ ተቀባይነት የለውም።

https://www.facebook.com/105146947885320/posts/pfbid038KbTuLaPFrKB68qvu2fgtwvXtwsm86JPY7HBdk3QpfmqBnuPCDxrStE99Wdptoibl/
ፈጣሪ ሀገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይጠብቅ
እናት ፓርቲ
ሐምሌ ፳፪ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
732 viewsedited  07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 10:31:54

511 views07:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 15:12:55 #ማኅቀፈ_እሳቤ_የጎሳ_ፖለቲካ_መዘዙና_የልጆቻችን_ኢትዮጵያ
በዶ/ር ኤርሲዶ ሌ.
ሰዓት ዛሬ፣ ረቡዕ 11:30 -12:30 ብቻ
ኹሉንም አማራጮች ተጠቅማችሁ ግቡ፣ ለሌሎችም አዳርሱ።

Join Zoom Meeting
https://us06web.zoom.us/j/3370247620?pwd=UmhvSWNSZDFIUjRhbTNYakh6cUFqUT09

Meeting ID: 337 024 7620
Passcode: thinking13
706 views12:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-18 19:23:35
#ሌላ_የድል_ዜና!
ፓርቲያችን #እንኳን_ደስ_አለን_ይላል። ገጻችንን ይውደዱ፣ ያጋሩ

https://www.facebook.com/105146947885320/posts/pfbid021Vp7S2zzN5xinBP7KQRqDv3ppti5ZQFco2vNMvmwe1oF6gz6HCqucni2xmh3g5d3l/?app=fbl
4.3K views16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-17 19:31:14
#ኢትዮጵያ_ስታሸንፍ_ፓርቲያችን_ቀዳሚው_ተደሳች_ነው። #እንኳን_ደስ_አለን ይላል!
ገጻችንን #ይወዳጁ፣ ለሌች #ያጋሩ

https://www.facebook.com/105146947885320/posts/pfbid0cyLC53pvbjpfLmf2NbcdkXPkpy68wdSt34ijAWfCudvPtjWfKJrfAsJRDdFhQoSSl/?app=fbl
4.2K views16:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ