ለአቅም ማሻሻያ ስራ ሲባል የሚቋረጥ የሃይል አቅርቦት
በባሌ ዞን በሚገኙ አንዳንድ ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት አየጨመረ በመምጣቱ ከሮቤ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በሚወጡ ኃይል ማሰራጫ መስመሮች ላይ የኃይል መጨናነቅ ችግር አስከትሏል፤ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ከኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የሚወጡ መስመሮችን አቅም ማሻሻያ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
ስለሆነም ችግሩ እስኪፈታ ድረስ በሮቤ፣ ጎባ፣ ሲናና፣ አጋርፋ ከተሞችና አካባቢዎቻቸው እንዲሁም በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲና አካባቢው የምትገኙ ደንበኞቻችን የኃይል አቅርቦቱን በፈረቃ ለመስጠት የተገደድን መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et