በኮንታና ዳውሮ ዞኖች የምትገኙ ደንበኞቻችን
ከመጋቢት 06 ቀን 2015 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በዳውሮ ዞን አባ ከተማ ላይ በሚገኝ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ በደረሰ ብልሽት በዳውሮ እና በኮንታ ዞን ባሉ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦል፡፡
በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን በጅማ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሰራተኞች በማከፋፈያ ጣቢያው የደረሰውን ብልሽት አስተካክለው እንደጨረሱ በፍጥነት አገልግሎቱን የምንሰጥ መሆኑን አውቃችሁ በትግስት
እንድትጠባበቁ እናሳውቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ለበለጠ መረጃ ይህንን ድረ-ገፅ፡ http://www.eeu.gov.et