የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ጋር እራት በሉ። ፕሮፌሰሩ ቀን በነበራቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቆይታ ተማሪዎቹ የተሳፈሩባቸው ባሶች በመግባት ጭምር የጎበኙ ሲሆን በእራት ሰዓት በነበራቸው ቆይታ " የጉዟቸውን ሁኔታ ማየት፣ የሚበሉትን በልተን ደህንነታቸውን ማረጋገጥ ስለሚገባን ያንን እያደረግን ነው። ወላጆች የልጆቻቸው ደህንነት ሳያሳስባቸው በሙሉ ልባቸው እንዲተማመኑብን እንፈልጋለን" ብለዋል። ሚኒስትሩ ከተማሪዎች ጋር በነበራቸው ቆይታ ተማሪዎችን አበረታተዋል። የህይወት ልምዳቸውንም አጋርተዋል። ትምህርት ሚኒስቴር ! 490 views18:15