Get Mystery Box with random crypto!

#Update የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች #የመጨረሻ ቀን የፈተና መር | EBS TV NEWS

#Update

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች #የመጨረሻ ቀን የፈተና መርሀ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ዛሬ ፈተናቸውን የሚያጠናቅቁት ተማሪዎች ከነገ ጀምሮ ወደየመጡበት አካባቢ የሚደረጉ ይሆናል።

የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች እንዲሰጥ ከመደረጉ በላይ አንዳንድ ተቋማት ኩረጃን ለመከላከል ከመጀመሪያው ቀን አንስቶ የደህንነት ካሜራዎችን ሲጠቀሙ እንደነበር ለማውቅ ተችሏል።

የደህንነት ካሜራዎችን ተማሪዎች በግቢ ውስጥ ያላቸውን እንቅስቃሴ እና በፈተና ክፍል ያለው የፈተና ስርዓት ለመከታተል ነው ጥቅም ላይ እያዋሉ ያሉት።

ዘንድሮ ከታዩ በጎ በጎ ጅምሮች በተጨማሪ እንደ መጀመሪያ ጊዜም ስለሆነ #ክፍተቶች የነበሩ ሲሆን እነዚህን በቀጣይ የምናነሳቸው ይሆናል።

ትምህርት ሚኒስቴርም ፈተና እንዳለቀ አጠቃላይ የነበሩ አፈፃፀሞችን ላይ መግለጫ እንደሚሰጥ ተነግሮናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን ፤ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናቸውን እንዳይፈተኑ እና ጥለው እንዲወጡ የሚያበረታቱ የተለያዩ አክቲቪስት ነን የሚሉ አካላት ፣ የማህበራዊ ትስስር ገፆች መኖራቸውን ተመልክተናል።

የተማሪዎችን ህይወትን የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ ለማድረግ የሞከሩም ብዙ ናቸው ፤ ድርጊቱ በነገ የሀገር ተረካቢ ልጆች ላይ ትልቅ ተፅእኖ ስላለው ቢታታረም መልካም ነው።

ገና ፈተናቸውን ያልወሰዱና ወደ መፈተኛ ተቋማት የሚገቡ በርካታ ተማሪዎች በመኖራቸው ያሉ ክፍተቶች እንዲታረሙ ለማደረግ መረባረብ እንጂ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ተማሪዎችን መረበሽ ፍፁም ተገቢ አይደለም።

ፎቶ ፦ አርሲ ዩኒቨርሲቲ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ

@EBS_TV_NEWS