ውድ ወላጆች፣ የ2015ዓ.ም የትምህርት ዘመን የነባር ተማሪዎች ምዝገባ የሚከናወነው ከሰኞ ሐምሌ 4/2014ዓ.ም እስከ ቅዳሜ ሐምሌ 16/2014ዓ.ም ብቻ መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን። ትምህርት ቤቱ ዘወትር ከሰኞ - ዓርብ አግልግሎት የሚሰጠው ከጥዋቱ 2:30 - 10:00 ፤ ቅዳሜ ከ 2:30 - 6:00 መሆኑን አውቃችሁ ምዝገባውን እንዲሁም የሩብ ዐመት ክፍያ የልጅዎን አካውንት በመጠቀም በብርሃን ባንክ እንድትፈፅሙ ። ማሳሰቢያ: 1ኛ. በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ ያልተመዘገበ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ እንድታስመዘግቡ:: 2ተኛ. የባንክ ደረሰኝ ወደ ት.ቤት በሚያመጡበት ጊዜ የልጅዎን ሁለት ጉርድ (3x4) ፎቶግራፍ ይዘው በመምጣት ለት.ቤቱ እንዲያስረክቡ እናሳውቃለን። ከላይ የተጠቀሱትን መመሪያዎች ተግባራዊ በማድረጋችሁ በቅድሚያ እናመሰግናለን፡፡ 1.6K viewsedited 06:43