2022-06-27 14:29:04
ሰኔ 20 በኬልቄዶን አውራጃ በቂሣሪያ ሀገር የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ያለ እንጨት ያለ ጭቃና ውሃ በሦስት ደንጊያዎች ብቻ በተወደደ ልጇ አጅ የታነጸችበት ዕለት ነው ።
#ሕንጸተ_ቤተ_ክርስቲያን_ዘእግዝእትነ_ማርያም
ጌታችን ባረገ በስምንተኛው ዓመት
ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ወደ ፊልጵስዩስ ገብተው በክርስቶስ ስም አሳምነው ብዙ አሕዛብን ካጠመቁ በኋላ ቤተ ክርስቲያን ሊሠሩላቸው ወደዱ፡፡
በዚህ ጊዜ ርእሰ ሐዋርያት እያለ እኛ መሥራት አይገባንም ብለው በሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ መልእክት ላኩበት፡፡ እርሱም ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር መጥቶ ከቅዱስ ጳውሎስ እና ቅዱስ በርናባስ ጋር በኢየሩሳሌም ተገናኙ፡፡
በዚያም በአንድነት ሱባዔ ይዘው ከቆዩ በኋላ ጌታችን የሞቱትን አስነሥቶ፣ ያሉትንም ጠርቶ ቅዱሳን ሐዋርያትን በፊልጵስዩስ አገር ሰብስቦ ‹‹በእናቴ በድንግል ማርያም ስም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚሠራዉን የአብያተ ክርስቲያናት ሥራ ላሳያችሁ፤ ሥርዓቱንም ላስተምራችሁ ሰብስቤአችኋለሁ›› ብሎ ወደ ምሥራቅ ይዟቸው ወጣ፡፡
በዚያ ሥፍራ የነበሩትን ሦስት ድንጋዮችንም
የተራራቁትን አቀራርቦ፣ ጥቃቅኑን ታላላቅ አድርጎ
ቁመቱን በ፳፬፤
ወርዱን በ፲፪ ክንድ ለክቶ ለቅዱሳን ሐዋርያት ሰጣቸው፡፡
ከዚህ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያት ሰም እሳት ሲያገኘው እንዲለመልም፣ ድንጋዩ በእጃቸው ላይ እየተሳበላቸው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ሠርተው ፈጽመዉታል፡፡
ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑ የተሠራዉም
ጌታችን በዐረገ በ፲፱ኛው፤
እመቤታችን በዐረገች በ፬ኛው ዓመት ሰኔ ፳ ቀን ሲኾን፣ በ፳፩ኛው ቀን (በማግሥቱ) ኅብስት ሰማያዊ፣ ጽዋዕ ሰማያዊ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ወረደ፡፡ ጌታችንም ከእመቤታችን ጋር ከሰማየ ሰማያት መጥቶ እመቤታችንን ታቦት፤ ሐዋርያትን ልዑካን አድርጎ፣ እርሱ ሠራዒ ካህን ኾኖ ቀድሶ ካቈረባቸው በኋላ
"#ከዛሬ_ጀምሮ_እናንተም_እንደዚህ_አድርጉ " ብሎ አዝዟቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡
( መጽሐፈ ስንክስር የሰኔ 20 ፣ መጽሐፈ ግስ ወሰዋሰው)
ንጽሕት በድንግልና ፣ ሥርጉት በቅድስና
እመቤታችን ወላዲተ አምላክ
ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ትሰውረን
ሠዓሊ ዲ/ን ጌታባለው አማረ
ሰዓሊ ቀሲስ አማረ ክብረት እና እኔ ዲ/ን ጌታባለው አማረ ልጃቸው በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማን ከቀኖና ስርዓትን ከትውፊት የጠበቁ ቅዱሳት ስዕላትን ሰዓልያን
@deacongetabalewamare
@deacongetabalewamare
301 views11:29