Get Mystery Box with random crypto!

የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል ጠቅላይ መምሪያ _ Commandos and Airborne Head Quarter

የቴሌግራም ቻናል አርማ commandoandairborneheadqurter — የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል ጠቅላይ መምሪያ _ Commandos and Airborne Head Quarter
የቴሌግራም ቻናል አርማ commandoandairborneheadqurter — የኮማንዶና አየር ወለድ ኃይል ጠቅላይ መምሪያ _ Commandos and Airborne Head Quarter
የሰርጥ አድራሻ: @commandoandairborneheadqurter
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.37K
የሰርጥ መግለጫ

Addis abeba Ethiopia

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 19:44:17 ሸኔ

ከወራሪው የህወሓት ኃይል ጋር የተሰለፉ በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች ተማረኩ

የህወሓት ወራሪ ኃይል ሰሞኑን ጥቃት በከፈተባቸው የአማራና የአፋር ግንባሮች ከቡድኑ ጋር ተሰልፈው ሲዋጉ የነበሩ በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች መማረካቸው ታወቀ፡፡

የህወሓት ወራሪ ኃይል በአማራና በአፋር ግንባሮች ጥቃት ከመክፈት ጎን ለጎን በተለያዩ አካባቢዎች ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጋር በመነቀናጀት ሽብር ለመፍጠር እየሠራ እንደሚገኝ የጠቆሙት ምንጮች፤ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአሸባሪነት ከተፈረጀው የሸኔ ቡድን ጋር በገባው ስምምነት መሠረትም በተለያዩ ግንባሮች የቡድኑን ታጣቂዎች አሰልፏል፡፡

በተለይ በቆቦ ከተማ ወረራ የፈጸመው ህወሓት የሸኔ ታጣቂዎችን ከፊት በማሰለፍ ወደ ፊት ለመግፋት ቢሞክርም በሀገር መከላከያ ሠራዊትና በጥምር ጦር በተሰነዘረበት መልሶ ማጥቃት ከፍተኛ ኪሳራ እንደደረሰበት የተገለጸ ሲሆን፤ በርካቶችም ተማርከዋል፡፡ ከምርኮኞችም መካከልም በርካታ የሸኔ ታጣቂዎች መኖራቸው ታውቋል፡፡

ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶችና ከውስጥ ባንዳዎች ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ  ቀውስ ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ህወሓት በተለያዩ ግንባሮች ጥቃት ከመክፈት ጎን ለጎን  በየክልሎች የሚገኙ ታጣቂዎች የሎጀስቲክስ፣ የፋይናንስና የመሣሪያ ድጋፍ እንዲደርሳቸው እገዛ እያደረገ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡

ቤተሰብ ይሁኑ!

https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
335 viewsedited  16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 10:10:08
ነሐሴ 25  ቀን 2014 ዓ.ም

በፈተና ነጥራ የወጣች ሀገር ኢትዮጵያ!!

ሀገራችን ኢትዮጵያ ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ፈተናዎች ያጋጥሟታል። ኢትዮጵያን ፈተናዎች አላዳከሟትም ይልቁንም ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ሆና ወደፊት እንድትቀጥል አበርትቷታል።

ኢትዮጵያ ወርቅ ነች። ወርቅ በእሳት ነጥሮ አምሮና ደምቆ እንደሚወጣው ሁሉ ኢትዮጵያም በፈተናዎች አልፋ ለዘመናት ታፍራና ተከብራ ኖራለች ትኖራለችም።

ኢትዮጵያ ፈታኞቿ የውጭ ጠላቶቿ ናቸው። እነዚህ ኃይሎች ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ሀገራችንን ፊት ለፊት ገጥመው ማሸነፍ እንደማይችሉ ከታሪክ መዝገብ የተረዱ በመሆናቸው  በባንዳና ተላላኪዎች አማካኝነት ፍላጎታቸውን ማሳካት ይፈልጋሉ።

በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች የሚጋለበው አሸባሪው የህወሓት ቡድንም እነሱ ያልተሳካላቸውን ሀገር የማፍረስ ህልምቸውን ተቀብሎ መቃዠት ከጀመረ ሰምበትበት ብሏል ብቻ ሳይሆን ከርሟል።

ኢትዮጵያን ፊት ለፊት ገጥመው የሆኑትን እና የሚሆኑትን የሚያውቁት የውጭ ጠላቶቻችን የወስጥ አንድነታችን ተበጣጥሶ አሸባሪውን ለማንገስ ዳክረዋል።

ወርቅ በእሳት ነጥሮ ወርቅ እንደሚሆነው ሁሉ ኢትዮጵያም በፈተናዎቿ ነጥራ የምትወጣ እንጂ ጠላቶቻችን እንደሚያስቡት የምትፈረካከስ ሸክላ አይደለችም።

የጀግኖች አባቶቹ ልጆች የሆነው ጀግናው የመከላከያ ሰራዊታችን የተረከባትን ሉአላዊ ሀገር ከጠላት እና ከባንዳ ተከላክሎ ለቀጣዩ ትውልድ የማሸጋገር ታሪካዊ ኃላፊነት ያለበት ኃይል ነው።

ለዚህም ሠራዊታችን የገጠመንን ጠላት በማንኛውም ጊዜ እና ሠአት በመንግስት በሚሠጠው አቅጣጫ መሠረት  ጠላትን በማደባየት ታሪካዊ ኃላፊነቱን ይወጣል።

#ኢትዮጵያ በጀግኖች ልጆቿ ታፍራና ተከብራ ትኖራለች!!
ቤተሰብ ይሁኑ!

https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
484 viewsedited  07:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 08:52:07
ኢትዮጵያ ወደ ሶስትዮሹ የህዳሴው ግድብ ድርድር ለመመለስ ዝግጁ መሆኗን ገለጸች

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት ስር ለሚካሄድ ድርድር ዝግጁ መሆኗን የገለፁት በሱዳን የኢትዮጵያ ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ ናቸው።

አምባሳደር ይበልጣል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በተለይም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ከተቀሰቀሰው ጦርነት ጋር በተያያዘ መቀመጫቸውን ካርቱም ለሚገኙ ብዙሃን መገናኛዎች መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው ዓለም አቀፍ ማሕበረሰብ የተጀመሩ የሰላም ጥረቶችን በመተው ጦርነት በጀመረውና በሽብረተኝነት በተፈረጀው ህወሓት ላይ ጫና እንዲያሳድር ጥሪ አቅርበዋል።

ተቋርጦ ረጅም ወራትን ስላስቆጠረው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ጉዳይ የተጠየቁት አምባሳደር ይበልጣል ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት ስር ወደሚካሄድ የሶስትዮሽ ድርድር ለመመለስ ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል።

ቤተሰብ ይሁኑ!

https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
459 viewsedited  05:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 18:11:05 ነሐሴ 24 ቀን 2014 ዓ.ም

"........
የማንጨበጥ ነበልባል-እሳት ነን ለጠላታችን
ፍሙ ከርቀት ይፋጃል- ብረት ያቀልጣል ክንዳች
ኢትዮጵያ በእኛ ደም ደምቃ-በአፅማችን ፍላጽ ተማግራ
እንደ ታፈረች እንድትኖር-ከዘመን ዘመን ተከብራ፤
.........."

ይህ ስንኝ ከጀግናው መከላከያ ሠራዊታች መሪ መዝሙር ላይ ተቀንጭቦ የቀረበ ነው!!

ሠራዊታችን የተሠጠውን ግዳጅ በአስደናቂ ብቃት ፈፅሞ  የሚያሳይ፤ ከፍተኛ ወታደራዊ የማድረግ ብቃት ያለው፣ የዘመኑን የጦርነት አቅሞች በሚገባ ተጠቅሞ በድል ላይ የሚረማመድ፤ በስነ-ልቦናዊና ሞራላዊ ዝግጁነቱ ጠንካራ የአሸናፊነትን መንፈስ የታጠቀ ነው።

የውጭም ይሁን የውስጥ ጠላቶቻችን በከንቱ ይዳክራሉ እንጂ ከአይበገሬው ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን እና የጥምር ኃይሎቻችን ፊት የሚቆም አንዳችም ምድራዊ ኃይል የለም።

#አሸናፊነት መለያችን ነው!!
ቤተሰብ ይሁኑ!

https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
559 viewsedited  15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 19:29:51
ጀግኖቻችን ባለቀይ ቦኔት የቁርጥ ቀን ልጆች

በሁሉም በጦር ግምባሮች ሽንታሟን ወያኔ አይቀጡቅጣት እየቀጡ ይገኛሉ። በጀግናው መከላከያ ሃይላችን ድል አድራጊነት የሚጠራጠር ካለህ እሱ/እሷ ያለጥርጥር ኢትዮጵያዊ አይደለም/ችም። 101% ድሉ የጀግናው መከላከያ ሃይላችን ነው።

ድል ለቀያይ ነብሮቻችን ኮማንዶዎች ይሁን

ቤተሰብ ይሁኑ!

https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
630 viewsedited  16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 14:40:53
መከላከያ ሰራዊት አሸባሪውን ቡድን እንደ አመጣጡ አፀፋዊ ምላሽ እየሠጠውና እየደመሰሰው እንደሚገኝ አስታወቀ!!

የአገር መከላከያ ሠራዊት ካለፈው የኅልውና ዘመቻዎች የጠላትን አሠላለፍ በውል በመገንዘብ አሸባሪውን የህወሓት ቡድን እንደ አመጣጡ አፀፋዊ ምላሽ እየሠጠው እና እየደመሰሰው እንደሚገኝ አስታወቀ።

ሠራዊታችን የድል ሠራዊት ነው በሚል ባወጣው መግለጫ በየትኛውም ቦታና ጊዜ፣ አስቸጋሪ መልክአ ምድርንም ሆነ የአየር ፀባይ ተቋቁሞ ግዳጁን በድል አድራጊነት የሚወጣው ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ጠላትን በአስተማማኝ መመከት የሚችል ኃይል መሆኑን አረጋግጧል።

ሠራዊቱ ከራሱ ይልቅ ሕዝብን ያስቀደመ፣ ለሀገር እና ለሕዝብ ራሱን አሳልፎ የሠጠ ብሔራዊ ኩራታችን ነው ብሏል።

ጠላቶቻችን ሕዝባዊ ባህሪውን በውል ስለሚገነዘቡ ህፃናትንና ሴቶችን ከፊት አሰልፈው ክፍለ ዘመን ባለፈበት ጦርነት በሕዝብ መአበል መዋጋታቸው የሠራዊታችንን አይበገሬነትና ጀግንነት ጠንቅቀው ስለሚያውቁት እንደሆነ ገልጿል።ጠላት ለዜጎቹ ደንታ እንደሌለው ባሳየው በዚህ የኋላ ቀር ጦርነት ሠራዊታችን በከፍተኛ ጥንቃቄ እና የኃላፊነት መንፈስ ግዳጁን እየተወጣ እንደሆነ በማመልከት አሸባሪው ህወሓት በለኮሠው እሳት መልሶ እየለበለበው እንደሚገኝ መከላከያ ሰራዊት አስታዉቋል።

ቤተሰብ ይሁኑ!

https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
738 viewsedited  11:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 14:11:09 ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም

"አየር ኃይሉ መክፈል የሚገባውን መስዋዕትነት ሁሉ ከፍሎ ኢትዮጵያ ታፍራና ተከብራ እንድትኖር ለማድረግ በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል።"
፦ ሌተናል ጀኔራል  ይልማ መርዳሳ

የኢፌዲሪ አየር ኃይል አካዳሚ በኤሌክትሮኒክስ፣ በአውሮፕላን አካል እና ሞተር ጥገና እንዲሁም በመሰረታዊ የአቪዬሽን ሙያ  ያሰለጠናቸውን የሰራዊት አባላት አስመርቋል።

በምርቃ ስነ -ስርዓቱ ተገኝተው በትምህርታቸው ብልጫ ላመጡ ሰልጣኞች ሰርተፍኬትና የማበረታቻ ሽልማት በመስጠት መልዕክት ያስተላለፉት የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጀኔራል ይልማ መርዳሳ ሲሆኑ አየር ኃይሉ ከሀገራዊ ለውጡና  ከተቋማዊ ሪፎርሙ በኋላ  የዝግጁነት አቅሙን ለማሳዳግ በሰው ኃይል ግንባታ፣ በዘመናዊ ትጥቆች እና ቴክኖሎጂ ብሎም ሰፋፊ የውጊያ መሰረተ ልማቶችን በማሟላት በትኩረት መስራት መቻሉን ገልፀዋል።

ተመራቂዎች  ያለንበትን  ወቅት በመረዳትና የተማራችሁትን ሙያ ወደ ተግባር በመቀየር ሀገራዊ ግዴታችሁን መወጣት አለባችሁ ሲሉ አሳስበዋል።

አየር ኃይላችን መከፈል የሚገባውን መስዋዕትነት ሁሉ በመክፈል ኢትዮጵያ ታፍራና ተከብራ እንድትኖር ለማድረግ  በላቀ የዝግጁነት ደረጃ ላይ ይገኛል ሲሉም አረጋግጠዋል ።

ለታላቅ ሀገር ታላቅ ተቋም በመገንባት ብሎም  ብቃትና ጥራት ያላቸውን ባለሙያዎችን በማፍራትና የኢትዮጵያን ጠላቶች ድባቅ በመምታት አየር ኃይሉ የጀግኖች መፍለቂያ  መሆኑን በተግባር እያስመሰከረ እንደሚገኝም ዋና አዛዡ ተናግረዋል ።

የኢፌዲሪ አየር ኃይል አካዳሚ አዛዥ ኮ/ል ገዛኸኝ ነጋሽ በበኩላቸው በአስተሳሰብና ክህሎት ብቁ የሆነ የሰው ኃይል በመፍጠር ዘመኑ የሚጠይቀውን ዕውቀት መሸከም የሚችል ፓይለትና ቴክኒሽያን እንዲሁም ሌሎች ሙያተኞችን በማፍራት  በአካዳሚው በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።

የአካዳሚ አዛዡ አክለውም በቀጣይ ኮሌጁን በቴክኖሎጂ ይበልጥ በማዘመን ከአፍሪካ ቀዳሚ የአቪዬሽን ተቋም ለማድረግ በትጋት እየሰራን እንገኛለን ብለዋል ።

ከተመራቂ ሙያተኞች መካከል አንዳንዶች በሰጡት አስተያየት ዘመኑ የሚጠይቀውን የአቪዬሽን እውቀት መቅሰማቸውን ጠቁመው በዚህም የሚጠበቅባቸውን ሁሉ በማድረግ ሀገራዊ ግዳጃቸውን በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ቤተሰብ ይሁኑ!

https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
589 viewsedited  11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 14:11:02
523 views11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 07:56:33
ነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም

ሠራዊታችን የድል ሠራዊት ነው !!

በየትኛውም ቦታና ጊዜ ፤ አስቸጋሪ መልክአ ምድርንም ሆነ የአየር ፀባይ ተቋቁሞ ግዳጁን በድል አድራጊነት የሚወጣው ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን ጠላትን በአስተማማኝ መመከት የሚችል ኃይል ነው።

መከላከያ ሠራዊታችን ከራሱ ይልቅ ህዝብን ያስቀደመ፤ ለሀገር እና ለህዝብ እራሱን አሳልፎ የሠጠ ብሔራዊ ኩራታችን ነው። ጠላቶቻችን ህዝባዊ ባህሪውን በውል ስለሚገነዘቡ ህፃናትንና ሴቶችን ከፊት አሰልፈው ክፍለ ዘመን ባለፈበት ጦርነት በህዝብ መአበል መዋጋታቸው የሠራዊታችንን አይበገሬነትና ጀግንነት ጠንቅቀው ስለሚያውቁት ነው።

በመሆኑም ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን ካለፈው የህልውና ዘመቻዎች የጠላትን አሠላለፍ በውል በመገንዘብ አሸባሪውን የህወሓት ቡድን እንደ አመጣጡ አፀፋዊ ምላሽ እየሠጠው እና  እየደመሰሰው ይገኛል።

ጠላት ለዜጎቹ ደንታ እንደሌለው ባሳየው በዚህ የኋላ ቀር ጦርነት ሠራዊታችን በከፍተኛ ጥንቃቄ እና የኃላፊነት መንፈስ ግዳጁን እየተወጣ ያለ ሲሆን አሸባሪው ህወሓት በለኮሠው እሳት መልሶ እየለበለበው ይገኛል።

ድል ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን!!

ቤተሰብ ይሁኑ!

https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
581 viewsedited  04:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 19:35:58 ወዳጄ ውጊያው ከህወሃት ጋር ብቻ ከመሰለህ ተሳስተሃል!!!

ህወሃት በመቶ ሺዎች የትግራይን ህዝብ ደመከልብ ካደረገች ጥቂት ወራት በኋላ ዳግም ወደ እልቂት የትግራይን ህዝብ የምትገፋው ማን የልብ ልብ እየሰጣት ይመስልሃል
የእጅ አዙር ጦርነት ያወጀችብን እኮ ግብጽ ናት!
ይህንን በማስረጃ ላስረዳህ ማስረጃ አንድ

ግብጽ ታሪካዊ ጠላቴ ኢትዮጵያ ናት ያለችው ዛሬ አይደለም። የህልውናዋ መሰረት የሆነው አባይ በኢትዮጵያ እጅ መሆኑን ጠንቅቃ ስለምታውቅ ኢትዮጵያ ከጠነከረች ውሃውን ለራሷ ልትጠቀምበት ትችላለች የሚለው እንቅልፍ ይነሳታል። ስለዚህ የተከፈለው ተከፍሎ ኢትዮጵያን ለማመስ ቀን ከሌት ትሰራለች። ማስረጃ ሁለት

የግብጽ ከፍተኛ ባለስልጣናት ቀጥታ ከኢትዮጽያ ጋር ጦርነት አንገጥምም፤ ኢትዮጵያን ከውስጥ መበጥበጥ፣ ጠላቶቿን በገንዘብም በመሳሪያም በማገዝ ከውስጥ ገዝግዘን እንጥላታለን ሲሉ ሁላችንም ሰምተናል። በዚህ ደግሞ ህወሃት ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሰይጣንም ጋር ቢሆን እናብራለን፤ ካስፈለገ ሲኦልም ድረስ እንወርዳለን ብሏል። ይህንን የህወሃት የክህደት ጥግ ለማገዝ ከግብጽ በላይ ማን ይመጣል። ህወሃት ኢትዮጵያን አፈርሳለሁ በሚል ለተነሳበት አላማ ሲኦልም መውረድ ሳያስፈልገው አጠገቡ ግብፅን አግኝቷል፤ ክህደት! ክህደት! ክህደት!  ማስረጃ ሶስት

ሰሞኑን ጀግኖቹ የሰማይ አናብስት የአየር ሃይላችን ለህወሃት መሳሪያ ሲያደርስ ቀልቦ ዶግ አመድ ያደረገውን አውሮፕላን ጉዳይ መቼም ሰምተሃል! በል ስለሱ ልንገርህ ስማኝ!
አውሮፕላኑ የግብጽ አንቶኖቭ ነው! ህወሃትን እንደ ፈረስ የምትጋልበው ታሪካዊ ጠላታችን ግብጽ ለህወሃት የላከችው መሳሪያ ነው። የተነሳው ደግሞ ሌላኛዋ ግብጽ እየተጠቀመችባት ከምትገኘው ከሱዳን ሰሜናዊ አካባቢ፤ መሮዌ ከተማ ነው!  ህወሃት አንደኛውን ሃቁን ነግሮናል! ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከሰይጣንም ጋር አብራለሁ ሲኦልም ቢሆን እወርዳለሁ ብሎናል! እንደ ፈረስ በታሪካዊ ጠላታችን እየተጋለበ የአይናችንን ብሌን ኢትዮጵያን ሲያፈርስ ቁጭ ብለን የምናይ መስሎት ነው?

እንደውም መንግስት ይህንን ኢትዮጵያን ለዘመናት ተጣብቶ የጭካኔ ጥግ ክህደቱን በተግባር እያሳየን ያለውን ህወሃት ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ያስወግድ! ኢትዮጵያ እፎይ የምትለው ከውስጧ የሚነክሳትን ህዝቧን በጭካኔ የሚጨፈጭፈውን ያረጀ ያፈጀ ቡድን ስታስወግድ ነው!  በህወሃት መነከስ በቃን!

ቤተሰብ ይሁኑ!

https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
626 viewsedited  16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ