2022-08-09 00:17:49
እባካችሁ ይነብብ
ተነሡ
የእግዚአብሔር አገልጋዮች ትጥቃቸውን ሲጥሉ ምድር በክፋት ትያዛለች። እየሆነ ያለውም ይሄው ነው። አማኞች የምድር ጨው ተብለው ነበር፥ ዓላማቸውን ሲዘነጉ ግን አልጫነቱ ባሰ።
የምድራችን መፍትሄው ወንጌል እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ ሀቅ ነው። ግን ማን ወንጌልን ይስበክ!? ነፃ የሚያወጣውን ወንጌል ማን ለትውልዱ ያድርስ!? አሁን አሁንማ ሰው ከተማ ብቻ የሚኖር ይመስል አገልጋዮች ከከተማ አልወጣ ብለዋል። የሚጮኸውም እዛው ነው። ይህም ሆኖ የተለወጠ ሰው ይኖር ይሆን!? እንጃ!
ወንጌል በሞራል፣ በሞቅታ ሳይሆን በሕይወት ቢሰበክ ኖሮ ስንት ህዝብ ወደ እግዚአብሔር መንግስት በተጨመረ ነበር።
ግን ምን ዋጋ አለው ወደ ውስጥ የማይገባ ነጥሮ የሚመለስ ባዶ ጩኸት ብቻ ሆነ።
አገልጋዮች ሆይ፦ "ማንን እልካለው?" የሚለው የእግዚአብሔር ድምጽ አሁንም እየጮኸ ነው። ከምቾታችሁ ውጡና የእግዚአብሔርን ቃል አንሱ። ከምን አገባኝ ስሜት ውጡና በሕዝብ ላይ የተጫነውን የክፋት አሰራር በኢየሱስ ስም ገስፁ። የጨለማው አሰራር ከምድራችን እንዲወገድ ጉልበታችን መሬት ይንካ። የትውልድን ደም ሊያፈስ፣ ነፍስ ሊቀጥፍ የወጣ የክፋት ሰይፍ ወደ ሰገባው እንዲመለስ ወደ እግዚአብሔር እንጩህ።
ሃይማኖተኝነት መቼም ቢሆን መፍትሔ ሆኖ አያውቅም። መፍትሄው መንፈሳዊ አማኝ መሆን ነው። ክርስቶስ በምድር ላይ ሲመላለስ የገሰጸው እምነት ማጣትን፣ ያደነቀውም እምነትን ነው። ስለዚህ ይህን ዘመን ለመሻገር በእምነት ወደ እግዚአብሔር እጅን ማንሳት ያስፈልጋል።
አማኝ ሲፀልይ እንጂ ሲያሸብር አያምርበትም። እቃ ጦሩ ፀሎት፣ መጽሐፍ ቅዱስ እንጂ ድንጋይ አይደለም። አማኝ የእግዚአብሔር ሥራ የበዛለት እንጂ ጊዜውን በአሉባልታ የሚያባክን ስራ ፈት አይደለም።
ወገኖቼ መከሩ ብዙ ነው ገና አልተነካም ፥ ሰራተኞቹ ግን ጥቂቶች ናቸው። ያላመነው ሳይሆን አምኖ የነበረውም ወደ ኋላ እየተመለሰ ነውና እንነሳ።
ተነሡ የቃሉን ብርሃን አብሩ፣ ብርሃን ባለበት ጨለማ አይሰለጥንምና!
እግዚአብሔር ምድራችንን ይፈውስ!
መፍትሄው ወንጌል ነው!
1.4K views21:17