Get Mystery Box with random crypto!

በዚህ ሳምንት ከሚወጣው ቃልኛ መፅሔታችን የተወሰዱ ሀሳቦች በሀገራችን ብዙ ጊዜ ስራ እንደሌለ ተደ | Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር

በዚህ ሳምንት ከሚወጣው ቃልኛ መፅሔታችን የተወሰዱ ሀሳቦች

በሀገራችን ብዙ ጊዜ ስራ እንደሌለ ተደርጎ ይወሰዳል። ከዛ ብዙ ሰው ተመርቆ ስራ የለም ብሎ በማመን ቁጭ ይላል። ለምን ቁጭ አልክ ሲባል ስራ ስለሌለ የሚል ምላሽ ይመልሳል።ይህ የማህበረሰባችን መሰረታዊ የዕይታ ችግር ነው። በተመረቅኩበት ስራ አላገኘሁም ስለዚህ ስራ የለም የምትል ከሆነ  ቅጥርን እንደ ትልቅ ስኬት እየቆጠርክ ነው ማለት ነው። ስራ የለም ብለው የሚያምኑ ብዙ ሰዎች ዝቅ ብለው የመስራት ስነልቦና ያላዳበሩ ሰዎች ናቸው።በውጪው አለም ሁለትና ከዛ በላይ ዲግሪ ይዘው መኪና እጥበት የሚሰሩና ቤተሰባቸውን የሚረዱ ህልማቸውን በገንዘብ የሚረዱ ብዙ ሰዎችን ማየት የተለመደ ነው። ስለዚህ ምን እንጀምር? ምን እንስራ? በዝቅተኛ ካፒታል የሚጀመሩ ስራዎች ምንድናቸው? እንደ ክርስቲያን የግል ስራዎን መጀመር እንዴት ይቻላል? አቅማችሁን እንዳትጠቀሙ ያደረጋችሁ ምንድነው? የሚለውን በስፋት እንመለከታለን . . .
በነቢይ መሳይ አለማየሁ


ታሪክን ፣ ባህልን፣ቀኖናን ፣ አስተምህሮን፣ ወግን በትክክል በተገቢው ሁኔታ በአፍሪካ የወንጌላዊያን ክርስትና ባለመተላለፉ ምክንያት በቀደምት ተሐድሶአዊያን ያልታሰበ ባዕድ ሀሳብ፣ ለነገሮች ያለ ምልከታ፣ ባህል ፣ወግ እንዲሁም ህግ ፍፁም የሚቃረን መንገድ በሀገራችንም ብሎም በአፍሪካ እየተመለከትነው ያለነው ስርዓት አልበኝነት በፕሮቴስታንቲዝም እንቅስቃሴ ውስጥ ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ሆኗል። . . .
በቢንያም አዲሱ


ማዳመጥ ግን ጥረት ይጠይቃል። በቀላሉ አይመጣም። በአንድ ጀምበር የማዳመጥ ጥበብን አንማረውም። ጥሩ የማዳመጥ ስሜት ማዳበር ከጊዜ ወደጊዜ የተሻሻለ ይሆናል፣ ነገር ግን ጥረት ማድረጉን የሆነ ቦታ መጀመር ይኖርብናል። . . .
በአቤኔዘር አለማየሁ


ጠያቂነታችን ከመኖር አላማችን ጋር የተቆራኘ መሆን አለበት።  ሁላችንም አጥርተን ባንረዳዉም  የምንኖርለት አላማ አለን ታዲያ አላማችንን መገንዘብ የምንችለዉ ለምን ተፈጠርኩ? በእኔ መኖር ዉስጥ ሊከፈት የሚገባዉ የትዉልድ በር ምንድነዉ? እነዚህና መሳል ጥያቄዎችን የጠያቂነት መብታችንን ተጠቅመን  መጠየቅ ስንጀምር ለተፈጠርንለት አላማም መኖር እንጀምራለን። . . .
በኤደን ቶሎሳ

ወረተኝነት ሄድ መለስ የሚል ስሜት ነው፤ ሞቅ ቀዝቀዝ የሚል አቋም፤ ከፍ ደግሞ ዝቅ የሚል መዋዠቅ ነው፤ እንዲህ ወይም እንዲያ ብለን እርግጠኛ የማንሆንበት መልክ ነው፡፡ በቆመበት የማናገኘው እንደ ጥላ የሚዞር፣ እንደ አየር የማይጨበጥ ነፋስ ነው፡፡ ስር ነቀል ፈውስ የሚሻም ደዌ ነው፡፡ ሳይታወቅበት ቤተክረስቲያን ውስጥ መሽጎ ቅዱሳንን የሚያስረመጠምጥ ነው፡፡ . . .
በመጋቢ ስንታየሁ በቀለ

እና ሌሎች ፁህፎች

ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር አድርጉ

ቃልኛ 9ኛ አትም
በዚህ ሳምንት

@KALTUBE
@KALTUBE
@KALTUBE
@KALTUBE