Get Mystery Box with random crypto!

(የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን)✝️

የቴሌግራም ቻናል አርማ chralaiso — (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን)✝️
የቴሌግራም ቻናል አርማ chralaiso — (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን)✝️
የሰርጥ አድራሻ: @chralaiso
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 571
የሰርጥ መግለጫ

ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
የገሀነም ደጆች አያናውጧትም
እ...ና...ታ...ች...
አ...ት...ታ...ደ...ስ...ም፡፡ ይህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ የሆነውን የህይወት ቃል ጌታ እግዚአብሔር በገለጠልን ፀጋ መጠን የምንካፈልበት ሲሆን!
" ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤"ቲቶ 2÷11 @lllala26

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-03 22:59:55 { አቡነ እጨጌ ዮሐንስ ዘጠገሮ} ~በጥቂቱ ታሪካቸው..
ያነበበብ አሜን ይበል!።
ጠገሮ ፃድቅ አቡነ እጨጌ ዩሐንስ ዘጸገሮ፦....... አባታችን የተወለዱት በኢየሩሳሌም አውራጃ ልዩ ስሙ ሳሬራ በሚባል የካቲት 28 ተፀንሰው በወራሀ ህዳር 28 ለ29 ሌሊት ተወለዱ (ህዳር29) ተወለዱ ፣የአባታቸው ስም ዲላሶር ሲባል የእናታቸው ስም ደግሞ እምነ ፅዩን ይባላል። ወላጆቻቸው እግዚአብሔርን የሚፈሩ ደጋግ ፃድቃኖች ናቸው ፃድቁ አባታችን ገና በአምስት አመታቸው ሳሉ
ወላጆቻቸው ወደ እግዚአብሔር ቤት ይዘዋቸው ሲሄዱ ፍቅሩ ወልዳ ስለ ማርያም ተመልክተው መሳቅ ጀመሩ እመቤታችን ድንግል ማርያም ከምስሉ ወጥታ በምን
አውቀህኝ ነው ብላ አቅፋ ሳመችሁ ከእንግዲ በኃላ የልጄ አገልጋይ ትሆናለህ ኑሮህም እንደ መላዕክት ይሆናል በአንተ ምክንያት ብዙ ሰዎች ይድናሉ በምድር ላይም 500 ትኖራለህ ብላ ባርካው ተሰወረች። ከዚያችም ቀን ጀምሮ አባ ዩሐንስ ለክርስቶስ ተላልፎ ተሰጠ 50 ዓመትም በበረሃ ሲጋደል ኖሮ ከ50 ዓመት በኃላ በደመና ተጭኖ በመላዕኩ ቅዱስ ገብርኤል መሪነት ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ
መጡ። ፃድቁ አባታችን በአቡነ ተክለሃይማኖት ዘመን መጨረሻ የመጡ ሲሆን ምንኩስና ከደብረ ሊባኖስ ገዳም ተቀብለው ለ50 ዓመት በፆምና ፀሎት በተጋደሉ ቆይተዋል። አባ ዩሐንስ ወደ ተዘጋቸላቸው ምድር በቅዱስ ገብርኤል
አሳሳቢነት ወደ ጠገሮ መጡ። ይህ ገዳማቸው የሚገኘው በሰሜን ሸዋ በመንዝናይፋት ክልል መዘዞ በሚባል ቦታ ሲደርሱ በእግር 1 ሰዓት ከተጓዙ በኃላ የሚገኝ ሲሆን
አስደናቂ የፃድቁ የእጬጌ ዩሐንስ ገዳም ነው።አባታችን ተጋድሏቸው ሳሉ ሰዎች በክፋት ተነሱባቸው ሰይጣን በእነርሱ አድሯልና እንዴት እንደሚያጠፋቸው ይማከሩ ጀመር ሊገድሏቸው ፈልገው ቅድስናቸው በሁሉ ዘንድ
የታወቀ ነውና ፈሩ ለምን ከምንደራችን ከወንድ ያረገዘች ሴት ፈልገን በሐሰት እንክሰሳቸው ብለው ወርቅና ብር ለሴቷ ሰጥተው በአሰት ከእርሱ አርግዣለሁ ብላ እንድትናገር አደረጎት አባታችንን በሕዝብ ፊት በአሰት ተከሰሱ ፃድቁም አንቺ ሴት ከእኔ ነው ያረገሽው አሏት እርሷም አዎ ከአንተ ነው ልትክድ ነው እንዴ አለችሁ አባታችንም አዝነው በአንቺና በእኔ መካከል እግዚአብሔር ይፍረድ ሲሉ ወዲያው ለሁለት ተሰንጥቃ ሞተች የአገሩ ሰዎች ፈሩ ፃድቁም ምድሯን እረገሟት የተዘራው ዘር አይብቀልብሽ የተተከለው አይፅደቅ ብርድና ውርጭ ይፈራረቅብሽ ብለው ረግመዋት በደመና ተጭነው ወደ ሰሜን ጎንደር እስቴ ጉንደ ተክለተሃማኖት ሄዱ። አባ ዩሐንስ በመላው ኢትዮጰያ ዞረው ያስተማሩ ሲሆን ከቅድስናቸው የተነሳ በፀሐይ ላይ 50 ዓመት በጨረቃ ላይ 50 ዓመት በደመና ላይ 50 እንዲሁም አለም በክንፎ በመዞር በደመና ላይ 50 የኖሩ አባትም ናቸው ከሰው ተወልደው ከመላዕክት ተደምረዋልና በይፋት ጠገሮባለወልድ ፣በአፋር አዘሎ፣በመንዝ ፍርኩታ ኪዳነምሕረት፣በደብረ ሊባኖስ፣ በጉንደ ተክለሃይማኖት፤ሳፈጅ ዮሐንስ ብልጋ፤አለም በመዘር እና በሌሎችም ስፍራ በመዘዋወር በታላቅ ተጋድሎ በፆምና ፀሎት ቆይተዋል።ከሰማይ መስቀል የወረደላቸው ሲሆን ዛሬም በገዳማቸው የሄደ ሰው በወረደው በእጃቸው መስቀል እየተዳበሰ ቆመው በፀለዩበት ባሕር በፀበላቸው ይጠመቃል በተጨማሪም ይዞሀት በነበረው መቋሚያ ጀርባችንን እንዳበስበታለን ማየት ማመን ነውና ከምስሉ ተመልከቱ መጥታችሁ ገደሙን ማየት ነው ። ቆመው
ከፀለዩበት ባሕር ውስጥ ደረቅ አሸዋ ይወጣል በገዳማቸው አባ ዩሐንስ 500ዓመት ከኖሩ በኃላ እረፍተ ዘመናቸው ደረሰ መዳኒዓለምም ከ15 ነቢያት ከ12 ሐዋሪያት ሄሮድስ ያስፈጃቸው ከአርባ አራት ሺው ሕፃናትን አብርሃም ይሳዕቅ፤ያዕቆብን ሁሉንም ነገደ መላዕክትን፤ነበያት፤ሃዋርያትን፤ ጻድቃን፤ ሰማዕታትን አስከትሎ መጣ ለአባ ዩሐንስ ቃልኪዳን ሰጣቸው ስምህን የጠራ ገዳምህን የረገጠ፣መባ የሰጠ፣ቤተክርስትያንህን የሰራ ያሰራ የረዳ፣ገድልን የሰማ ያሰማ ያስተረጎመ፣ መታሰቢያን ያደረገ፣ እስከ10 ትውልድ እምርልሀለው ንስሀ ሳይገባ አይሞትም ልጅ መውለድ ባይችል ማህን ቢሆን እኔ ልጅ እሰጠዋለሁ የክርስትያን ማደርያ በሆነች ገነት(ደብረ ፂዮን)በብርሃን ቦታ አስቀምጠዋለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ሰጣቸው ገድላቸው በጥቂቱ ነው እንዲሁም ገድልህን በቤትህ ያስቀመጠ እርኩስ መንፈስ አይነካውም፣ክፉ አጋንት አይነካውም፣ቸነፈርና ወባ አይነካውም፣መላኢከ ጽልመት አይነካውም።በገዳምህ መነኩሴ ቢቀበር በሰማይ
ክንፍ አበቅልለታለሁ፣አይሁድም አረማዊም ያላመነ ያልተጠመቀ በገዳምህ መጥቶ ቢያርፍ ይቅር እልለሃለሁ እንደ መቃብሬ ጉልጎታ እንደተቀበረ አድርጌ እቆጥርልሃለሁ።
የነገርኳችሁ ከዚህ በኃላ ወደ ሰማይ አረገ አባ ዩሐንስ ሐምሌ 29 ቀን አረፉ። በጉንደ ተክለሃይማኖትም ተቀበሩ 157ዓመት በኃላ አንድ የበቁ ባሕታዊ ወደ መንዝ ሄደው የረገሟት መሬት እንድትቀደስ የተዘራው እንዲበቅል ከስውራን አባቶች ጋር በመሆን ግማሽ አፅማቸውን ከጉንደ ተክለሃይማኖት አውጥተው አርባሐራ መዳኒዓለም አጠገብ በላይ በፍሩክታ ኪዳነምሕረት መጋቢት 18 ፍልሰተ አፅሙ አረፈ ምድሪቷም ተባረከች የዘሩትንም አበቀለች ውርጩም
ብርዱም ቀነሰ ዝናብ አልዘንብ ሲል ሰብል የሚጨርስ አንበጣ ሲመጣ ታቦታቸው ወጥቶ ምዕላ ይያዛል ወድያውም መቅሰፍት ይርቃል ዝናብም ይዘንባል። ፀበላቸው ሽባ ይተረትራል ድውይ ፈዋሽ ከሰማይ የወረደላቸው መስቀልም ታምር ሰሪ ከባሕራቸው ደረቅ አሸዋ የሚወጣበት የጠገሮ ፃድቁ እጬጌ ዩሐንስ በረከት
ይደርብን አሜን!!!
18 viewszagol, 19:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 18:29:44
79 viewszagol, 15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 18:29:41 ኪዳነ ምህረት

ኪዳነ ምህረት እመቤት
ዳንኩኝ በፀበልሽ ባማላጅነትሽ
ነይ ወደኔ ዘወትር ስጠራሽ
ፈልጌ ሁሌ ስማፀንሽ
ህይወቴን ቀይሪያት አማልደሽ ከልጅሽ
ረጅሙ መንገዴ ይቅና በፊትሽ
ትሁን ነብሴ ታማኝ ለልጅሽ
እንዴት እረሳለው ያረግሺልኝን
መድሀኒቴን ወልደሽ የፈወስሺኝን
ቤቴና ህይወቴ
ትባረክ ባንቺ እመቤቴ
75 viewszagol, 15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 14:30:48 (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን) pinned a photo
11:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-02 14:30:19
እንግዲህ ስትበሉም ሆነ ስትጠጡ ወይም ማናቸውንም ነገር ስታደርጉ ሁሉንም ነገር ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉ።
79 viewszagol, 11:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 22:53:51
ወዳጄ እንደተራ ሰዎች ማርያም ታማልዳለች አታማልድም ከሚል ክርክር ውጣ አንተ እኮ ጥቅስ አንብበህ ሳይሆን በህይወትህ ተደርጎልህ ነው ያየኸው እና በፍፁም ከየማይመጥኑህ ሰዎች ጋር አትከራከር፡፡
100 viewszagol, 19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 21:04:25 (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን) pinned «ስለ ማርያም ብዙ ጊዜ ከኛ ሀይማኖት ውጪ ያሉ ሰዎች እናንተ ኦርቶዶክሶች ለማርያም ያላቹ ክብርና ፍቅር የተለየ ነው ይሉናል የተጋነነም ነው ይሉናል ።እስቲ ወደ ሁዋላ መለስ ብለን እናስታውሳቸው ። የሆሳዕና ዕለት ህዝቡ ግማሹ ልብሱን ግማሹ ዘንባባውን እያነጠፈ የነበረው እኮ ክርስቶስን አክብሮ እንኳን አንተ ይቅርና የተቀመጥክባት አህያ እንኳን መሬት አትነካም ሲሉ እኮ ነው ። እና እንስሳዋ አህያ ለ1…»
18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 21:04:17 ስለ ማርያም

ብዙ ጊዜ ከኛ ሀይማኖት ውጪ ያሉ ሰዎች እናንተ ኦርቶዶክሶች ለማርያም ያላቹ ክብርና ፍቅር የተለየ ነው ይሉናል የተጋነነም ነው ይሉናል ።እስቲ ወደ ሁዋላ መለስ ብለን እናስታውሳቸው ። የሆሳዕና ዕለት ህዝቡ ግማሹ ልብሱን ግማሹ ዘንባባውን እያነጠፈ የነበረው እኮ ክርስቶስን አክብሮ እንኳን አንተ ይቅርና የተቀመጥክባት አህያ እንኳን መሬት አትነካም ሲሉ እኮ ነው ። እና እንስሳዋ አህያ ለ1 ሰአት ለማይሞላ ጊዜ ክርስቶስ ስለተቀመጠባት ብቻ በዘመኑ የነበሩ ሰዎች ያን ያህል ካከበሯት 9 ወር ከ 5 ቀን በማህፀኗ ተሸክማ በድንግልና ወልዳ አቅፋ አጥብታ አሳድጋ ይዛ ግብፅ ተሰዳ ሲሰቀል አይታ ላነባችለት ይሄን ሁሉ ለሆነችለት እናቱ እኛ የዘመኑ ክርስቲያኖች ክብር ብንሰጥ ጥፋታችን ምንድነው ? እኛስ ለማርያም ክብር እንሰጣለን ። ከአባ ህርያቆስም ጋር ሆነን እንዲህ እንላታለን "ማርያም ሆይ እንወድሻለን ስለዚህም እናገንሻለን ፡ የህይወትን ምግብና መጠጥ ወልደሽ ሰጥተሽናልና "።
93 viewszagol, 18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 21:03:17 ህልሞቻችን

3 ዛፎች ነበሩ ። 2ቱ የቆሙ ሲሆኑ አንዱ ግን የወደቀ ነው። ከእለታት በአንድ ቀን ህልማቸውን ይነጋገሩ ጀመር ። አንደኛው እኔ ሳጥን ሆኜ የአለም ውድ እቃ አልማዝ እንቁ እንዲቀመጥብኝ እፈልጋለው አለ፣ ሁለተኛው ደሞ እኔ መርከብ ሆኜ የአለም ነገስታት እንዲጓጓዙብኝ እፈልጋለው አለ ፣ ሶስተኛው ደሞ እኔ ደሞ እኔ መድሀኒት ሆኜ ብዙዎችን ማዳን እፈልጋለው አለ ። ሶስቱም ህልማቸውን አውርተው ሲጨርሱ ዛፍ ቆራጮች መጡ የወደቀውን አነሱት ይዘውትም ሄዱ ። እሱም ሳጥን መሆን የሚፈልገው ነበር እነሱም ጠርበው የከብቶች መመገቢያ አድርገው ሰሩት።ሁለተኛውንም መጥተው ቆረጡት እሱም መርከብ መሆን የሚፈልገው ነበር እነሱም ጀልባ አድርገው ሰሩት ። ሁለቱም ዛፎች ተናደዱ ህልማቸው የተጨናገፈም መሰላቸው። ከአመታት ቡሀላም ክርስቶስ ተወለደ። እነሆም ቦታ ስላልነበር በከብቶች በረት ተወለደ። እናቱ ማርያምም በከብቶች መመገቢያ ውስጥ ጠቅልላ አስቀመጠችዉ። ያም የአለም ውድ ነገሮች ማስቀመጫ መሆን እፈልጋለው ያለው ነበር ፡ የውዶች ውድም የሆነው ጌታም ተቀመጠበት። ጌታም ሊያስተምር ሲሄድ በታንኳ ተጓዘ ፡ ያም ታንኳ ያ የአለም ነገስታት እንዲጓጓዙብኝ እፈልጋለው ያለው ነበር፡የነገስታት ንጉስም ተጓጓዘበት። ጌታም እንዲሰቀል ሲፈረድበት የቀረውን ዛፍ ቆርጠው አመጡ በሱም ሰቀሉት። እሱም ለብዙዎች መድሀኒት መሆን የፈለገው ዛፍ ነበር። እሱም መስቀል ሆኖ አለም ሁሉ ዳነበት። ሶስቱም ዛፎች ህልማቸው የተጨናገፈ ሲመስላቸው ፈጣሪ ግን ካሰቡት በላይ አድርጎ አሳካላቸው። ወዳጄ ህይወት መንገዷን የቀየረች ህይወትህም በችግር የተሞላ ሊመስልህ ይችላል። ዛሬ አንተን የሚያማርሩ ነገሮች ፈጣሪ አንተን የነገ ህይወትህን ለመስራት የሚጠቀምባቸው ንጥረ ነገሮች ናቸው ። ነገሮች ሲመሰቃቀሉ ምናልባት ቦታ ቦታቸውን እየያዙ ይሆናል። የማይገድል ችግር ሁሉ ያጠነክርሀል ።
237 viewszagol, 18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 08:52:09
101 viewszagol, 05:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ