Get Mystery Box with random crypto!

Care Arts✍️🎤🎨

የቴሌግራም ቻናል አርማ careartsss — Care Arts✍️🎤🎨 C
የቴሌግራም ቻናል አርማ careartsss — Care Arts✍️🎤🎨
የሰርጥ አድራሻ: @careartsss
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 838
የሰርጥ መግለጫ

ኢትዮጲያ በሚሏት የሚስኪኖች ሀገር
ሁሉም ሰው እረስቷት እኛ ብቻ ብንቀር
መቼም አናቆምም እሷን ብቻ ማፍቀር።
ғᴏʟʟᴏᴡ ᴏɴ ᴛɪᴋᴛᴏᴋ
https://tiktok.com/@bantegize21
በቻናሉ የሚቀርብ
#ግጥሞች
#ትረካ
#ታሪክን_የኋሊት
#ወጎች
#ድሮን_በትውስታ
#ልብወለድ
#ጠቃሚ_ምክሮች

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-06-07 00:46:17 የኬር አርትስ ቤተሰቦች ቲክቶክ ላይ ፎሎ በማድረግ ቤተሰብነታችሁን አሳዩኝ። አሪፍ አዝናኝ እና አስተማሪ ነገሮችን ይዤ ለመምጣት በሂደት ላይ ነኝ። ለጊዜው ጥሩ እና ደስ ይላሉ ያልኳቸውን የግጥም ስራዎች ለቅቂያለው እነሱን በማየት ተደሰቱልኝ።
https://tiktok.com/@bantegize21
https://tiktok.com/@bantegize21

ታዲያ Follow
Like
Share
Comment እንዳይረሳ ሁላችሁንም ፈጣሪ ያክብርልኝ።
151 viewsedited  21:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 22:39:43 "እንዴት?" አይባልም
ኤልያስ ሽታኹን
~ ~ ~ ~ ~

የትዝታ ዳሩን ይዤ ጥጉን መንገድ
ሳቋን ተደገፍኹኝ ደሞ ስንገዳገድ።

"እንዴት?" አይባልም::

የሄድኩት ቢቆጠር ሀገር ያሻግራል
ሳቋ ክንፍ አብቅሎ በኔ ልክ ይበራል።

"ለምን?" አይባልም::

የአንዳንድ ሰው ናፍቆት እንደእግዜር ዓይን
"እንዴት?" አይባልም
የአንዳንድ ሰው ሳቁ ይመሰላል ሰማይን::
"እንዴት?" አይባልም
የአንዳንድ ሰው ጠረን ይመስላል ህዋውን
"እንዴት?" አይባልም
ካቻምና ያወቁት ይሸታል እስካሁን።

ፍረድብኝ መዓት.....
ለትዝታ ትርጉም
ግጥም ብደረድር ማሕሌት ካልበቃኝ
አታንሳኝ ምጽዓት
በርታሁ ያልኩትን እሱ ነው ያስጠቃኝ።

ሰበሰብኹኝ ብዬ
ነፍሴን ልቤን እጄን ከትዝታ እሳት
ጭራሽ ናፈቀችኝ እንኳንስ ልረሳት።

እንዴት? አይባልም


"ዋነኛ አላማችን ጀማሪ የጥበብ ባለተሰጦዎችን ማበረታታት ነው"

━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ሼር ያድርጉ
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
252 views19:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-02 09:37:54
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች
እንኳን ለ1443ኛው የኢድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን !!

በዓሉ የሰለም፣ የፍቅር ፣ የጤና እና የተቸገሩ ወገኖቻችንን የምንጠይቅበትና ያለንን የምናካፍልበት ያማረ በዓል ይሁንልን።

ኢድ ሙባረክ!
መልካም በዓል!!

@CareArtsss
@CareArtsss
@CareArtsss
267 views06:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-25 19:24:55 ፍቅራችንን በልጦት ፣ ምድር ትርምሱ፣
ተስፋችንን ውጦት ፣ መለያየት ምሱ፣
እንደወጣን ቀረን፤
መ፟ለየት በረደን፤
ተፈጥሮ ሳይሞቀን፣
ሳንተያይ መሸ ፤ ሳንተያይ ነጋ ፤ በመተያያ ቀን።
አንቺ ከአስመራ ፤ ናፍቆትሽ ተኩሎ፤
እኔ ካ'ዲሳባ ፤ ያውም ካራት ኪሎ።
በተቃጠርንበት ፣ በዚያች ምጽዓት 'ለት፣
አጊኝቼ ልስምሽ ፣ የተሳልኩት ስለት፣
አልሠመረም መሰል…
ከቤቴ እንደወጣኊ ፣ ከቤት እንደወጣሽ፣
ምን ጋር ስ'ደርሺ ነው ፣ ተፈጥሮ የቀጣሽ?
እኔ…
በስልክ ካወራነው
ከነገርኩሽ ቦታ ፣ ኾኔ እየጠበኩኝ፣
አሻግሬ ባይሽ
ከወዲያ ወደዚኽ ፣ ድንበር ነው ተባልኩኝ።
አትመጪም ማለት ነው?
ድንበር ነው ምንድነው?
ድንበር ማለት ማነው? ወደኔ ያስቀረሽ?
ድንበር የሚባለው…
የድሮ ባልሽ ነው ፤ ያልነገርሺኝ ፈርተሸ።

እኔ…
እየጠበኩሽ ነው፤
በጎረምሳ ልቤ ፤ ባረጀው አቋሜ፤
ዘመናት ቢነጉዱም
ሌላ ቀን አልቆጥርም ፤ ቀጠሮሽ ላይ ቆሜ።
ነይልኝ የኔ ቀን ፤ ነይ የኔ ጨረቃ፤
ፍቅሬ ገና ልጅ ነው ፤ ዕድሜዬ እያበቃ።
ከጊዜ በኋላ ፣ ድንገት የኾነ ቀን
ከዚኽ ቦታ መጥተሸ፣የሌለኹኝ መስሎሽ ፣ ከቶ አታቀርቅሪ፤
በስልክ ያልኩሽ የለም ፤ አርጅቼ ይኾናል ፤ ምልክት ቀይሪ።
አለኹኝ ቆሜያለኊ ፤ በቀጠሮ ነፍሴ፣
ያኔ ስንቀጣር ፣ ስወጣ የነገርኩሽ ፣ ተቀይሯል ልብሴ፤
በይ አድፏል በወዜ፤
ተቀዷል በጊዜ፤
ተቦጫጭቆ አልቋል፤
ተቆራርጦ ወድቋል፤
የቀጠርሽኝ ዕለት ፣ የለበስኩት ጫማ
ከእግሬ ላይ ደርቋል ፤ ቀልጦ እንደሻማ።
ጣቴ ተጠባብቆ፤
ተረከዜ ደቆ፤
አይመጣም ፤ አይሄድም ፤ አልመጣም ፤ አልሄድም፤
ልብ እግር አይደለም አይሰነጠቅም።
የቀጠርሽኝ ዕለት ፣ ጺሜን ባነሣውም ፣ ለዚያ ዘመን ውበት፣
አድጎ ይበጠራል ፤ ቀለሙን ቀይሮ ፣ ተውጧል በሽበት።
የቀጠርሽኝ ዕለት…
ይዤ የወጣሁት ፣ አበባውም ደርቋል፤
ዘመን ተለውጦ ፣ ሌላ አበባ ፈክቷል፤
ምልክት እንዲኾን…
በስልክ የነገርኩሽ ፣ አበባ ይዣለኊ፤
ደርቆ ረግፎብኛል ፤ ባዶ እጄን ግን አለኊ፤
ባዶ እጄን ግን አለኊ ፤ ከነሙሉ ልቤ ፣ በርታልኝ እያልኩት፤
አልጸድቅ ያለኝን ፣ ቀጠሮ መውደዴን ፣ ተስፋ እያጠጣሁት፤
አለኹ ከዚኽ ቦታ ፤ እንደ ተራ ጥሬ፤
ከቅዱስ ቃል እኩል ፣ ቃልሽን ቆጥሬ።
ዕድሜዬን ገብርኩኝ ፤ ለሌላ ሴት ላልኾን፤
ከመቀመጥ ብዛት ፣ ላላፊው ላግዳሚው ፣ ምልክት እስክኾን።
ከጊዜ በኋላ ፣ ድንገት የኾነ ቀን…
ከዚኽ ቦታ መጥተሸ ፣ የሌለኹኝ መስሎሽ ፣ ከቶ አታቀርቅሪ፤
በስልክ ያልኩሽ የለም ፤ አርጅቼ ይኾናል ምልክት ቀይሪ።
ያልኩሽን በሙሉ ፣ ፀሐይና ውርጩ ሲፈራረቁበት፣
በመሸው ዕድሜ ላይ ፣ ቀን እየመሸበት።
ወዴትም ባልሸሽም ፣ ከዕድሜ ለመ፟ደበቅ፣
እንዳትደነግጪ!
አካሌ በሙሉ ፣ ደክሟል በመጠበቅ።
ተጣጥፏል ቆዳዬ፤
አይወርድም ዕንባዬ፤
ከንፈሬ አርጅቷል ፤ ላንቺ ለምውድሽ እንደተቀመጠ፤
አፌ ዳቦ ረስቷል ፤ ተስፋ እያላመጠ።
እኖራለኊ ላንቺ ፤ ኹሉን ተቀብዬ፤
ፈገግ እላለሁኝ ፤ ተፈጥሮ ነው ብዬ፤
ብዙ አላዳምጥም ፤ የመኪና ታምቡር፤
ጆሮዬ ደክሞብኝ
ለራሴ እዘፍናለኊ ፤ የሀገሬን መዝሙር።
ደምሥሮቼ ኹሉ
ቀን እየተመኙ ፣ ቀን የተነጠቁ፣
ነይልኝ ይመስላል!
በከንፈሬ መሐል ፣ የሞላው ሥንጥቁ።
የቀጠርሽኝ ዕለት…
የነገርኩሽ ጸጉሩ ፣ በዕድሜ ተሟሽቶ፣
ገፍቼው ይመስላል ፣ ወደኋላ ሸሽቶ።
ባረጀው አካሌ ፣ ከሐዘን እንዳለኊ
አርጅቼልሽ የለ ፣ ጺም መንካት ወዳለኊ።
የቀጠርሽኝ ዕለት…
ስሜ ስም ብቻ ነው ፤ ያኔ ስናፍቅሽ፤
ጋሼ ተጨምሯል ፤ አንቺን ስጠብቅሽ።
አንቱ ተባልኩልሽ ፤ ሠርክ ሳብሰለስል፤
የቀጠረኝ ድምጽሽ ፣ ሒድ ይለኝ ይመስል።
የቀጠርሽኝ ዕለት…
ያረኩት ቀለበት
ጠቦኝ ፣ ጠቦኝ ፣ ጠቦኝ ፣ ጣቴን አሳመመው፤
መቼ ትመጫለሽ? እስከዛ ላስታመው።
ከየትም የሚጮህ ፣ያ ሰላላ ድምጼ ፣ ከጭስ እንደዋለ፣
አርጅቼልሽ የለ!
አኹን ስተነፍስ ፣ በቃላቴ መሐል ፣ የኾነ ሳል አለ።
የቀጠርሽኝ ዕለት ፣ የነበርኩት ኹሉ ፣ ያደረኩት ኹሉ፣
ደብዛው እንኳን የለም፤ የነበረው ውሉ።
አለኹኝ ከቦታው ፤ አለኹ ከሰዓቱ፤
ቆጥረሽ አስረጂልኝ ፤
ስንት ቀን ኾኖኛል ከመጣሁኝ እቱ?
መቁጠር እኮ አልችልም!
ምልክቱ ኹሉ ዛሬ ተቀይሮ
በእርጅና በድካም ፣ ዙሪያ ተከብቤ፣
ዐይኔ እንደፈዘዘ ፣
ምልክት ይኹንሽ ፣ ተንቀልቃዩ ልቤ።
ከቶ አይቀርምና ፣ ላንቺም ማጎንበሱ
በቀጠሮ ቦታ ፣ የወደቀ ካየሽ ፣ ተጣሪ በስሱ።
እኔ ነኝ!
ባልሰማሽም እንኳን ፣
የሌለኹኝ መስሎሽ ፣ በዕንባ እንዳታመሪ፤
የኔ ውብ ፣ የኔ ዓለም ፤
አርጅቼ ይኾናል ፤ ምልክት ቀይሪ።
በነፋስ ቢበተን ፣ ሐሳቤ ፣ ሐሳብሽ፣
በድንበር ቢበትን ፣ ናፍቆቴ ፣ ናፍቆትሽ፣
የኔ ሰዓት ቆሟል ፤ ስንት ይላል ሰዓትሽ።
መቁጠር እኮ አልችልም!

ገጣሚ ኤልያስ ሽታሁን


"ዋነኛ አላማችን ጀማሪ የጥበብ ባለተሰጦዎችን ማበረታታት ነው"

━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ሼር ያድርጉ
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
255 views16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 09:20:35
''ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ▸ በዐቢይ ኃይል ወስልጣን ፤ አሰሮ ለሰይጣን አግአዞ ለአዳም ፤ ሰላም ▸ እምይእዜሰ ፤ ኮነ ▸ ፍስሐ ወሰላም''

◈ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን። ◈

◆ በዓሉ የሰላም የጤና እንዲሆንላቹህ እንመኛለን ◆

መልካም በዓል ለሁላችሁም


"ዋነኛ አላማችን ጀማሪ የጥበብ ባለተሰጦዎችን ማበረታታት ነው"

━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ሼር ያድርጉ
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
211 viewsedited  06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-07 20:32:56 ትወጅኛለሽ።
~ ~ ~ ~ ~ ~
ማረፊያ ያጣ
የደሀ ወንድ ክንፍ
ባለጸጋ ዓይንሽ ላይ እርፍ።

ዓይንሽ ከለለኝ ዓለሙን
ዓይንሽ ጋረደኝ ወጀቡን
በሽፋሽፍትሽ ቀዝፌ
ብሰምጥም ያው ትርፌ።
(አንቺ ካለሽ)

ባላውቅበት ፍቅር ደርዙን
እጠጣለሁ ናፍቆት መርዙን::
(ይገለኝ እንደሁ
አያለሁ።)

ተሰናብቼ መኖሬን
እንደመነኩሴ ቀብሬን
ቀድሜ ገባሁ ኑዛዜ
በኔ ዘንድ የለም ቀን ጊዜ።

ደሞ
የወደድኹሽ ቀን ለካድኩት
የናፈቀሽኝ ቀን ለተውኩት
የመሰንበትን ጣጣ
መኖር ይሉት መተት ባንቺ ዕምነት ወጣ።
እኔ
መውደድሽን ከአንደበትሽ ለመስማት ሳጣጥር
እጅሽ ነገረኝ ሚስጥር
ትወጅኛለሽ።

እንደልጅ ነኝ
እኖራለሁ ተጠልዬ
ብጎለምስ
እሞታለሁ ሁሉ ጥዬ
:
ገመድ ሳይሆን ቅብጠትሽን ተንጠልጥዬ ።

ትወጅኛለሽ።

ኤልያስ ሽታሁን

"ዋነኛ አላማችን ጀማሪ የጥበብ ባለተሰጦዎችን ማበረታታት ነው"

━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ሼር ያድርጉ
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
287 views17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-04 20:39:44
416 views17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-13 15:07:07 ቀን ሳወራሽ ውዬ
የልቤን ለልብሽ
ድብርት ወረረኝ
አመሻሽ ላይ ሳጣሽ
ቀን ከሌት ባወጋሽ
አይን አይንሽን እያየው
ከቶ መች ጠግቤሽ
መች ሰለችሻለው

ባንተጊዜ
፲፩/፭/፳፻፲፬ ዓ.ም
362 views12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-06 16:16:11 ሰንበት
ካንቺ ለመሰንበት፡፡
* * * * * *
በድንኳን ምድራችን
በዕንባ የተከልነው
ሀዘኑ በደሉ ገፍቶ ያመነነው
አይለካም እንጂ የልቡ ቁዘማ
የሰው ልጅ አይደርስም እንደሀዘኑማ፡፡


ሻርኩኝ ሰንበት
ጎባጣሽን ዓይቼበት
አትሻሩ ብሎ ያዘዘውን ጌታ
ሳስብሽ ዋልኩበት በወንጌሉ ቦታ፡፡
እጠየቅ እንደሆን አንቺን ላየሁበት
እከሰስ እንደሆን አንቺን ላሰብኩበት
እነሆኝ ጌታዬ
አለሁ ለማጣቱ
ሰኞን መቀማት ነው የሰንበት ቅጣቱ?
እሷ ሰኞዬ ነች
እሷ ነገዬ ነች
(አታሳዝንህም?)
ማንም የራሱን ነው ቢበላውም ቢያክም
እሷን ግን እይልኝ
ለኔ አጎንብሳ የተጫናት ሸክም፡፡
ትዝታ ያጎብጣል
እንደሰም ያቀልጣል፡፡
በየንግሡ ዕለት
አይቻለሁና ሰባራን ስትገጥም
የኔን ምስኪን ማራት
ህመም ቀን አይመርጥም፡፡
በበሽተኛ ዓይን
ከጥያቄው ያልፋል ያንዳንዱ ቀን መልሱ
ሰንበት አይደለም ወይ የሰው ሳቅ በራሱ?

ሰው ይሰግድልሀል
ዓለሙ በሙሉ ባንተ ስለዳነ
ዓይኗን ክፈትልኝ በበደሌ ብዛት ስለተከደነ፡፡

ምንተስኖት አንተ
እስመዐልቦ አንተ
ሰው ያርግድልሀል
አጣፍጥልኝ ብሎ የኮመጠጠውን
እኔ ግን እላለሁ
አትፈውስም ወይ? ፍቅር ያጎበጠውን፡፡


ገጣሚ ኤልያስ ሽታኹን


"ዋነኛ አላማችን ጀማሪ የጥበብ ባለተሰጦዎችን ማበረታታት ነው"

━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
ሼር ያድርጉ
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
⇨ @CareArtsss ⇨ @CareArtsss
━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━━
538 views13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-03 22:18:30 Care Arts pinned a video
19:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ