#MettuUniversity
በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ወደ መቱ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ግንቦት 03 እና 04/2014 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።
ወደ ተቋሙ ስትሄዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦
• ከ8ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃዎች
ዋናውንና ኮፒው
• የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ውጤት ዋናውና ኮፒው
• የቅርብ ጊዜ ጉርድ ፎቶግራፍ (4)
• ብርድልብስ፣ አንሶላ፣ የትራስ ልብስ
• የስፖርት ትጥቅ
የስማችሁ ቀዳሚ ፊደል ከ'A-D' የሆነ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች እና የስማችሁ ቀዳሚ ፊደል 'A' የሆነ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ብቻ ምዝገባችሁ የሚከናወነው በበደሌ ካምፓስ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ የሚመጡ ተማሪዎችን የማያስተናግድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።
@campus_group_ethiopia
@campus_group_ethiopia