Get Mystery Box with random crypto!

Classk Kiya❤️❤️❤️

የቴሌግራም ቻናል አርማ blaak_69xxx — Classk Kiya❤️❤️❤️ C
የቴሌግራም ቻናል አርማ blaak_69xxx — Classk Kiya❤️❤️❤️
የሰርጥ አድራሻ: @blaak_69xxx
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 145
የሰርጥ መግለጫ

Best photo 🙈🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
Best music ⛤💝💝💝💝
Best voice 🙇❤❤❤❤❤
Best video ✔💋💋💋💋
Fenny video
Comment 💪 @Blaak_kineg
Best group ............t.me/iscoduryew ..........🍬🍬🍬
🇪🇹🇪🇹
Chanale ❤69 xxx @Blaak_69xxx

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-19 20:40:02 Voice message
1.1K views...1669 kiya Tesfu fikadu, 17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 08:47:26 አፄ ምኒልክ ለብዙ ጊዜ ሲብሰለሰሉበትና ሲጨነቁበት የነበረ አንድ ጉዳይ ነበር። ዙፋን ፣ አልጋ፣ ቀጣዩ ንጉሥ አልያም ቀጣዩ የኢትዮጵያ እጣ ፈንታ ልንለው እንችላለን። ንጉሱ ታመው በአልጋ ላይ ከዋሉ በኃላ ብዙ ጊዜ ይጨነቁ እንደነበርና በልጅ እያሱ ላይ የሹመት[የንግስና ] ሥርአተ መንግስቱን አሳልፎ ለመስጠት ልጅ እያሱም ገና ልጅ መሆናቸውና የቤተመንግስት ጠባይና ሥርዓትን በደንብ ያልተረዱ መሆኑ ብዙ እምነት ለመጣል ተቸግረው ይብሰለሰሉ ነበር። የሆነው ሆኖ ምርጫ ያጡት ንጉሱ ይሁንታቸውን በኑዛዜ አስተላለፉ። ፀሀፉ ትዕዛዝ ገበረ ሥላሴም በታሪክ ነገስት ዘዳግማዊ መጽሐፍ ውስጥ እንደሚከተለው አስፍረውታል። ~አዲስ አበባ ጃን ሜዳ ጉባኤ ተደርጎ ስለ ልጃቸው ኢያሱ አልጋ ወራሽነትና አገዛዝ ያዘዙት ቃል ተነበበ። ቃሉም ይህ ነው። "ያገሬ የኢትዮጵያ ሰዎች ልጆቼ ወዳጆቼ እግዚአብሔር የገለጠልኝን ምክር ልምከራቹ ምክሬም በልባቹ እንደሚፀና ተስፋ አደርጋለሁ። ዓፄ ቴዎድሮስ በሞቱ ጊዜ ከርሳቸው ጋር የነበረውን ሰው ሁሉ ያንዱን አገር አንዱ እደርባለሁ አንዱን ገድዬ እኔ ጌታ እሆናለሁ እያለ ሁሉም ሳይረባ ተላልቆ ቀረ። ከዚያም በኋላ የዓፄ ዮሐንስም ሰው የሆነውን የምታውቁት ነው።ባገር በሽታ ሳይገባበት ሌላ ጦርነት ሳያነሳበት በምቀኝነት እርስ በርሱ እንደተላለቀ አይታችሁበታል። አሁንም ልጆቼ ወዳጆቼ አንዱ ባንዱ ምቀኝነት ይቅር ።ያአንዱን አገር አንዱ እደርባለሁ እንዳትባባሉ ።እኔ እስካሁን በፍቅር እንዳኖርኋችሁ እናንተም በፍቅር ተስማምታቹ በፍቅር እንድትኖሩ እለምናችኋለሁ።እናንተ አንድ ልብ ከሆናችሁ በምቀኝነት እርስ በርስ ተዋግታቹ ካላለቃችሁ በቀር አገራችንን ለሌላ ለባዕዳን አሳልፋቹ አትሰጡም።ክፉ ነገርም አገራችንን አያገኛትም ።ንፋስ አይግባባችሁ አገራችንን በያላችሁበት በርትታችሁ ጠብቁ።ወንድሜ ወንድሜ ተባባሉ። ይህን ምክር መፃፌ እኔማ በእግዚአብሔር ፈቃድ ይህንን ያህል ዘመን ገዛሁ።ነገር ግን ሰው ነኝና ለዘላለም አልኖርም።እኔም እንደምመኘው ልጄን ኢያሱን እግዚአብሔር ካቆየላቹ አብራችሁ አገራችንን ጠብቋት።ከዚህ ከፃፍኩት እኔም ሳለሁ ሆነ ካለፍሁ በኋላ ከፈቃዴ የወጣ ሰው ረግሜአለሁ። በሰማይም በምድርም የተረገመ ይሁን" የሚል ነበር፡፡

ሹማምንቱና መሳፍንቱ የንጉሱን ቃል ለመተግበር ቢሞክሩም በልጅ እያሱ በኩል የነበረው የበሳል ዓስተዳደር ችግር ሀገሪቷን ወደ ሌላ ምዕራፍ አሸጋገራት አልያም የአርባ ዓመታትን ሌላ ቅርጽ ሰጥቶ አስጓዛት።

መልካም ንባብ

የቴሌግራም ቻናላችን @Blaak_69xxx

ያላችሁን ሀሳብ አስተያየት በፁሁፍ ለመቅረብ
የቴግራም ጉሩፓችን @iscoduryew

የሚፈልጉትን መፅሀፍ ለማዘዝ @Blaak_kineg

የቻናላችን ተከታይ ስለሆኑ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው ።

ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።
1.1K views...1669 kiya Tesfu fikadu, 05:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 08:47:26 ....
ብዙ የማውቃቸው ሰዎች ሀይማኖት ያላቸው ሲኦል እና ገነት አለ ስለተባሉ ነው። ከክፋት የሚቆጠቡት ሲኦልን ፍራቻ እንጂ መልካም መሆን ምንም ሽልማት የለውም ክፉ መሆንም ምንም ቅጣት የለውም ቢባሉ ለክፋት የሚግደረደሩ ናቸው። በሰውነት ሰው ስለመሆን ሳይሆን እግዚአብሔር ወይም አላህ ወይም ሌላኛው አምላክ በክፋታቸው ይቀጣናል ፤ በመልካም ስራቸው ይሸልመናል ብለው ስለሚያምኑ ነው ሚዛን የሚሰሩት። እስኪ እውነት እናውራ ከተባለ የብዙ ሀይማኖቶች መደምደሚያ ከሞት በኋላ ያለ ሽልማት ወይ ቅጣት ባይሆን ምን ያህል ሰው ሀይማኖት ይኖረው ነበር? ምን ያህል ሰው ቅዱስ የሚለውን ስራ ለመስራት ይጋጋጣል? ምን ያህሉስ ሰው ወደሀይማኖት ተቋማቱ እየሄደ አቴንዳንስ ያስመዘግብ ነበር?

ተስፋ ፍቃዱ

@Blaak_kineg
771 views...1669 kiya Tesfu fikadu, 05:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 08:47:26 "ስማ ! ኪብሬ" አለው ፤ ዶ/ር ክብረ በዓልን <ኪብሬ> ብሎ ነው የሚጠራው ። "ሰው ሆኖ መሞት ወዳጅ ሆኖ መለያየት አይቀርምና አንድ ነገር ልንገርህ ብዬ ነው " አለው ።
"ደግሞ ዛሬ ምን ልታመጣ ነው?" ሲል
"እየውልህ! አንተ ለእምነትህ አዳሪ፣ ፈጣሪን የምትፈራ ጥሩ ክርስቲያን ነህ ። እኔም በአላህ ላይ ያለኝ ኢማና ፣ ለነብዩ ያለኝ ክብር እንደምታውቀው ጥልቅ ነው። ሁለታችንም በእውነትና በቅንነት ባለንበት እየተጓዝን ነው" አለና ፈገግ ብሎ "ብቻ ከሁለት አንዳችን መጨረሻ ላይ ስሕተት ሁነን መገኘታችን አይቀርም።" ሲል ሁላችንም ከልብ ሳቅን።
"እና ምን አሰብክ?" አለው ዶ/ር ክብረ በዓል ።
"እኔ ትክክል ሆኜ ከአላህ ፊት ስቀርብና <ወደ ጀነት ግባ > ስባል አንተ ስሕተትኛ ሆነህ <ወደ ጀሃነም ሂድ> ስትባል <ቸሩ አላህ ሆይ ኪብሩን ጀነት አብረህ ካላስገባህ ብቻዬን አልገባም> እላለሁ ወይም ደግሞ አንተ ትክክል ሆነህ ክርስቶስ ፊት ስትቀርብ <ወደ ጀነት ግባ ፣ ነቢል ወደ ጀሃነም ይሂድ ሲባል <እሱንም ጀነት ካላስገባህ እኔንም ጀሃነም አስገባኝ" ትላለህ ። በዚህ መልክ ሁለታችንም safe እንሆናለን" አለው።
ንግግሩ የዶ/ር ክብረ በዓልን ብቻ ሳይሆን የኔንም እንባ አስመጣው።
ድንገት ክብረ በዓል ብድግ ብሎ ግንባሩን ሳመውና፦
"አይዞህ! በተለያዬ መንገድ ብንጓዝም በቅንነት እስከሆነ ድረስ ፈጣሪ ቅን ፍርዱን አይነሣንም" አለው። ......

እዛው እንደተቀመጥኩ ፍቅራቸውና ባልንጀርነታቸው ደንዳናው ልቤን ብስክስኩን አወጣው። ከዚያ በኋላ የሚነጋገሩትን ብዙም አልሰማሁም። በዚች ምሥጢራዊት ሀገር እንደነዚህ ያሉ ልበ ንጹሓን ሰዎች በመኖራቸው ነው ምንጮች የሚፈልቁት ፣ ወንዞች የሚፈሱት ፣ በደረቅ ሰማይ ደመና ዝናብ አርግዞ ጠለ-ምሕረት የሚዘንብ ፣ ሰማይ ያለምሰሶ የረጋው ፣ ምድር ያለካሥማ የጸናችው " እያልኩ በእጅጉ የመጽናናት መንፈስ ውስጤን አረሰረሰ።.....

ከሚተራሊዮን መጽሐፍ የተቆነጠረ
#ዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ

@Blaak_kineg
731 views...1669 kiya Tesfu fikadu, 05:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 22:55:54 ┄┉┉✽̶»̶̥ ••✿•• »̶̥✽̶┉┉┄
የነገን ማወቅ
ሚካኤል በላይነህ
@Blaak_kineg
┄┉┉✽̶»̶̥ ••✿•• »̶̥✽̶┉┉┄
686 views...1669 kiya Tesfu fikadu, 19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 22:38:14 ┄┉┉✽̶»̶̥ ••✿•• »̶̥✽̶┉┉┄
ደስተኛ መሆን
#ምክር
r @Blaak_kineg
┄┉┉✽̶»̶̥ ••✿•• »̶̥✽̶┉┉┄
669 views...1669 kiya Tesfu fikadu, edited  19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-07 16:28:46 ባጣሽ የምሞት መስሎኝ ስፈራ
ብቴጅ ደመቀ ህይወቴ አበራ
እንኳን ልጎዳ ልሰበር ልረግፍ
መቆም ተማርኩኝ ሰው ሳልደገፍ
ያለኔ አይኖርም ብለሽ ብቴጂ
አልቀረብኝም ቀረብሽ እንጂ
በገፋኝ ልብሽ አላዝንም ላፍታ
ይመጣል ሌላ በሄደው ፋንታ
የናቅሽው ልቤን ዳግም ልትረግጪ
ናፍቆኛል ብለሽ ከቶ እንዳትመጪ
ያለኔ አይኖርም ብለሽ ብቴጂ
አልቀረብኝም ቀረብሽ እንጂ
2.1K views...1669 kiya Tesfu fikadu, 13:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-05 23:25:14 ይሔ አንቺን አይገልፅም!
፨፨፨፨፨//////////፨፨፨፨፨
አዎ! ይሔ አንቺን አይገልፅም፤
ይሔ ያንተ ማንነት አይደለም።
ሰውኛውን የሰው ልጅ ባህሪ በመተው በሰዎች ውድቀት ከፍ ብሎ መታየት፣
በሌሎች ህመም መደሰት፣
በሰዎች የኋሊት ጉዞ ድል አድራጊነትን ማክበር የከባድ ምቀኝነት ህመም ነውና ልንጠየፈው ይገባል።
አዎ! ጀግኒት..! ክፋትን በክፋት መመለስ፣
የጎዳሽን ለመጉዳት መጣጣር፣
ጉዳቱን፣ ህመሙን መመኘት፣
ለሰበረሽ የስብራት መንገድ መፈለግ፣
ለጣለሽ ዳግም እንቅፋት ሆኖ መገኘት አንቺን አይገልፅም። ያንቺ ተሽሎ መገኘት የሚታወቀው ከወረዱት ጋር በመውረድ ሳይሆን ላለመውረድ በመታገለ፣ ከእነርሱም ተሽሎ በመገኘት ነው። ለጎዳሽ ጉዳትን አትመኚም፤ ያንቺን ስቃይ ማንም እንዲያየው ስለማትፈልጊ፤
ለጠላሽ፣ ለገፋሽ መጠላትን መገፋትን አትመኚም የመጠላትን፣ የመገፋትን ስሜት ስለምታውቂ፤
ላዋረደሽ መቼም ውርደትን አትመኚም ይልቅ ክብርን፣ ሞገስን ትመኚለታለሽ።
አዎ! ያንቺ መገለጫ ይሔ ነው። ጥላቻን በፍቅር መሻር፣ ክፋትን በበጎነት፣ ስብራትን በመልካምነት ማበስ።
አዎ! ጀግናዬ..! በሰው ስኬት መቅናት፣
በሰው ከፍታ መከፋት፣
በሰው ደስታ መናደድ፣
በሌላው ማማር፣ በሌላው መዋብ ማዘን በፍፁም ያንተ ማንነት አይደለም። እርሱን ለትንሾችና ለታሰሩት ተውላቸው፤ አንተ እራስህን በመልካምነት፣ በበጎነት፣ በቅንነት ነፃ አውጣ።
የሰው ልጅ ምርጫ ግሩም ነው ምንም እንኳን ሁሉም ለክፋቱ ምክንያት ባያጣም ለመልካምነት ሲሆን ግን ለክፉነት የተገኘው ያ በቂ ምክንያት መጥፋቱ ይገርማል። ምናልባት እጅጉን መልካምና ቅን የሚባለው ሰው ከማንም በላይ ተበድሎ፣ ተጎድቶ፣ ተሰቃይቶ ይሆናል፣ ነገር ግን ክፉ መሆን እየቻለ መልካምነትን መርጧል። ቀላል ስለሆ አይደለም፤ ጫና ስለሌለው አይደለም፣ ስሜቱን ማዳመጥ አቅጦትም አይደለም ቢታመምም መድሃኒቱ በጎነት እንደሆነ ስላመነ ነው፤
ቢሰበርም ጠጋኙ መልካምነት እንደሆነ ስለገባው ነው፤
ምንም ቢከፋ የሰው ደስታ ለእርሱ እረፍቱ እንደሆነ ስለተረዳ ነው።
አዎ! የክፋትን ጥግ ቢያሳዩህም አንተም ተሽለህ ለመገኘት የመልካምነትን ጥግ አስጎብኛቸው።
የቅስምን ስብራት፣ ጥልቁን ህመም ቢያሰሙህም የስብራቱን መድሃኒት፣ የህመሙን ፈዋሽ በጎነትን ከልብህ አካፍላቸው።
የጣለህን ተነስተህ አንተም ዳግም ብትጥለው መቼም ከእርሱ አትሻልም፤ ያንተ ተሽሎ መገኘት የሚታየው ከወደክበት ተነስተህ እርሱንም ይዘሀው መጓዝ ስትጀምር ነው።
ውብ ምሽት ይሁንልን!
2.1K views...1669 kiya Tesfu fikadu, 20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-05 23:24:26
#የመፅሐፍ #ጥቆማ
#የማይሰበረው_#የሕይወት #ታሪክ

አይበገሬው ሰው እንዴት ከጉዞው እንደተሰናከለ ወይም ነገሮችን እንዴት በተሻለ መልኩ መፈፀም ይችል እንደነበር በሩቁ ሆኖ አስተያየቱን የሚሰጠው ከዳር
ተደምጦ ትችቱንም የሚሰነዝረው በጉዳዩ ውስጥ ቦታ የላቸውም። በተግባር የፍልሚያ ሜዳ ውስጥ ገብቶ በጀግንነት ሲዋደቅ ሁለመናው በአቡዋራ ፣ በደምና በለብ ለጨቀየው ለራሱ ባለጉዳዩ ነው እውቅና የሚገባው :: በጥረት ውስጥ ስህተት እና ጉድለት አይታጣምና ፣ ስኬት ሊጎናፀፍ በልበ ሙሉነት ሲጣጣር ስህተት የፈጸመው ፤ ከጎዞው ደግሞ ደጋግሞ የተሰናከለው ፤ ያም ሆነ ግን አላማውን ከማሳካት ከመጣር የማይቦዝነው መቼም ቢሆን ጥረቱን የማይገታው ፤ ጥልቅ ስሜቶችንና ታላላቅ መስዋአነቶችን ጠንቅቆ በመረዳት ላመነበት ነገር ራሱን የሚሰዋው ፤ ከቀናው የላቀ ስኬት ድል በወጉ ለማጣጣም ፤ ካልሆነለት ደግሞ ድልንም ሆነ ሽንፈትን አይተው ከማያውቁት ድንጎጥ እና ፈሪ ነብሶች ተርታ አንድም ቀን ራሱን ላለማሰለፍ በፅናት እየታገለ እስከ ፍፃሜው የሚዋደቅ አይበገሬው ጀግና ነው። ክብር እና ሞገሱ ።

የጥንካሬ ምሳሌ የብዙ ሀሳቦች አመንጪ #የማይበገረው በትክክል የሚገልፀው ወደው አንብበው ጠንካራ ሚሆኑበት....



የቻናላችን ተከታይ ስለሆኑ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው።

ለንባብ መጎልመስ ሁሌም እንተጋለን።

1.5K views...1669 kiya Tesfu fikadu, edited  20:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-05 23:21:17 ... የፈተናው ማዕበል ሊውጠን ሲል፣ ወጀቡ ከልካችን ሲያልፍ "ተሻገሩ" ያለን ጌታ ከታንኳችን ከች ይላል፡፡ ያን ጊዜ ነገር ሁሉ ወደ ጸጥታ ይመለሳል፡፡ የመንግሥተ ሰማያት ጌታ በመርከባችን ቆሞ ማዕበልና ወጀብ፣
ንፋስና ባሕር የማወክ ኃይል የማናወፅ ጉልበት አይኖራቸውም፡፡ ችግራችንን፣ ጭንቃችንን፣ ሥጋታችንን እየረገጠ የመጣው ጌታ እስከታመንነው ድረስ እንደ ጴጥሮስ በባሕሩ ላይ ሊያቆመን፣ በጭንቃችንም
ላይ ሊያራምደን ይችላል፡፡ ከእምነታችን ማነስ የተነሳ መንሸራተትና መስመጥ ብንጀምር እንኳ ከፍቅር አባት የምንሰማው “አንተ እምነት የጎደለህ ስለምን ተጠራጠርህ?" የሚል አባታዊ ወቀሳ ብቻ ነው፡፡ ከዚያም ወሰን በሌለው የእርዳታ ክንዱ ስቦ መንጭቆ ያወጣናል፡፡ ...


....ይሁን እንጂ ይህንኑ በጎ አካሄድ ተተግኖ የሚሠሩ ታሪካዊ ሸፍጦች እዚህም እዚያም ይታያሉ፡፡ በሀገራችን በኢትዮጵያ በሌሎች አንዳንድ የዓለም ክፍሎችም የሚታየው ሀሠተኛ የታሪክ መሠረቶችን የማቆም ድርጊት
አሣፋሪ ነው። ይህ ተግባር ያለ በቂ መረጃ አልፎ አልፎም ያለ አንዳች መረጃ ከመፈፀሙም በላይ ዓላማውም መጻዒያቱን ጊዜ በፈለጉት መንገድ ለመተለም የተደረገ ይመስላል፡፡ በደገኛው የታሪክ ጥናት ውስጥ የሚሰነቀሩ
እንዲህ ያሉ ጥፋቶችን ነው እንግዲህ “ሰንኮፍ ያልኳቸው:: ...

....ቢቸግረው "መጣሁ ሜሪ” አለና መንገዱን ተሻግሮ ከአንድ ጎዳና ተዳዳሪ ጋር ያወራ ጀመር፡፡ ከዚያም እርሱንና ሁለት ሕጻናት አስከትሎ መጣ፡፡ ጎዳና
ተዳዳሪ ያልኩት ልጅ በዕድሜ የእኛ እኩያ ሲሆን ጸሐይና ንፋስ ገፁን አወይቦት ምንም ዓይነት ድምቀት አይታይበትም፡፡ እጅግ የነተበ ሱሪ ቢያደርግም አንዱ ታፋው ላይ በትልቁ ተቦጭቆ እርቃን እግሩ በሰፊው
ይታያል፡፡ በጣም ያደፈ ኤርጌንዶ ጫማም አድርጓል፡፡ ከመቆሸሹ ብዛት የለበሰው ቲሸርት ቀለሙ የማይታወቅ ሲሆን እላዩ ላይ የተበጣጠሰ ጃኬት ደርቦበታል፡፡ ጃኬቱ ቁልፍ ወይም ዚፕ ስለሌለው እንደበረደው ሰው በአንድ
እጁ ሁለቱንም ሳይድ አጣብቆ ይዟቸዋል። ዞማ የሚባል ዓይነት ጸጉር እንዳለው ሲያስታውቅም እንደሚገባ ስላልተያዘ ከፀጉሩ ጋር የሣር ቁርጥራጮች፣ አቧራና ጥጥ መሳይ የልብስ ቅሪቶች አብረው ይታያሉ፡፡ ...

መፅሐፍ የውስጥ ገፅ የተቀነጨበ
#የሳንኮፋ #ሰንኮፍ
ማርያማዊት ገብረመድኀን

የቴሌግራም ቻናላችን @azop78
ለንባብ መጎልበት ሁሌም እንተጋለን።

1.1K views...1669 kiya Tesfu fikadu, 20:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ