የወልድያ ከተማ ሠላማዊ እንቅስቃሴዋ እንደቀጠለ ነው።
ከወራሪው ቡድን ጋር የሚደረገው የጥምር ጦሩ ፍልሚያ አሁንም በሕዝባዊ ደጀንነት ታጅቦ እንደቀጠለ ነው። የወልድያ፣ የሐብሩ እና የሌሎችም ወረዳዎች ወታደራዊ ስልጠና የወሰደ ሁሉ ጥምር ጦሩ ጋር ለመቀላቀል ወደ ግንባር እየዘመተ ነው።
በወልድያ ከተማም ከጅቡቲ ወደብ የሚነሱ አገር አቋራጭ ተሽከርካሪዎችንም ከተለመደው ጉዟቸው ያስተጓጎላቸው ሁኔታ አልተከሰተም።
መረጃው የወልድያ ከተማ ኮሙኒኬሽን ነው
ከግንባር መረጃዎችን የሚያደርሰውን የቴሌግራም ገፅ ይቀላቀሉ:-
https://t.me/Bete_amharamedia