Get Mystery Box with random crypto!

Best Sport Ethiopia🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ bestsportet — Best Sport Ethiopia🇪🇹 B
የቴሌግራም ቻናል አርማ bestsportet — Best Sport Ethiopia🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @bestsportet
ምድቦች: ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.28K
የሰርጥ መግለጫ

ቤስት ስፖርት በኢትዮጵያና በሀገር ማዶ ስፖርታዊ ክንውኖች ዙርያ ትኩረት አድርጎ የሚሠራ ድረ ገፅ
✅የሃገር ቤትና የባህር ማዶ ትኩስ ትኩስ መረጃዎች
✅የተጫዋቾችና የአሠልጣኞች የስፖርት ሠዎች ያልተሠሙ ቃለ-ምልልሶች
✅የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ሙሉ መረጃ
✅ቁጥራዊ መረጃዎች እና ዳሰሳዎች
✅የጨዋታዎች ቀጥታ ሽፋን
ለሃሳብ ለአስተያየትዎ
0911478296
https://www.bestsportet.com

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-13 06:28:49
የማንቺስተር ሲቲው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በ2025 ከኢትሀዱ ክለብ ጋር ለመለያየት እያቀደ መሆኑን ማስታወቁ ይፋ ተደርጓል

የ52 አመቱ ካታሎናዊው የወደፊት እጣ ፈንታውን በተመለከት እስካሁን ድረስ ከውሳኔ ላይ ባይደርስም የውሀ ሰማያዊዮቹ ቤት ኮንትራት ውል ቆይታው ሲያበቃ ለመልቀቅ በማጤን ላይ ነው ተብሏል።

ፔፕ በቀጣይ የዩናይትድ ስቴትስ ወይም ብራዚል ብሄራዊ ቡድንን ሊረከብ የሚችልበት ሰፊ እድል እንዳለውም ተገልጿል።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
648 viewsYishak Belay, edited  03:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-13 06:26:11
አርሰናል እንግሊዛዊውን የዌስትሀም ዩናይትድ አማካይ ዴክላን ራይስ ክለቡ ለተጫዋቹ በጠየቀው 100 ሚሊየን ፓወንድ የዝውውር ሂሳብ ለማስፈረም መቃረቡ ተነግሯል

መዶሻዎቹ የዩሮፓ ኮንፍረንስ ሊጉን ዋንጫ ካነሱ በኋላ የክለቡ ሊቀመንበር ዴቪድ ሱሊቫን ኮከባቸው በክረምቱ ከክለቡ ጋር እንደሚለያይ እርግጠኛ ሆነው መናገራቸው ይታወሳል።

አርሰናል አስቀድሞ ራይስን ማስፈረም ተቀዳሚ ኢላማው አድርጎ መቆየቱ ይታወቃል።

የመድፈኞቹ ቀጣዩ ትልቁ ስራ የሚሆነው ከተጫዋቹ ጋር በግል ጥቅማጥቅም ዙሪያ መስማማት እንደሆነ ተዘግቧል።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
582 viewsYishak Belay, edited  03:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-13 06:22:42
ማንቺስተር ሲቲ በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቹ በተሰባሰቡበት የሶስትዮሽ ክብሩን በጎዳና በክፍት ባስ ላይ በመሆን አክብሯል

ከባድ ዝናብ በነበረበት እና ተቀጣጣይ ነገሮች ወደ ሰማይ በብዛት በተተኮሱበት ጥቂት የማይባሉ የቡድኑ ተጫዋቾች ከወገባቸው በላይ ያለ ልብስ ታይተዋል።

ዋና አሰልጣኙ ፔፕ ጋርዲዮላ በበኩሉ ከዚህ ቀደም እንዳደረገው ሲጋራ ሲያጤስ ታይቷል።ስነ ስርዐቱ በእለቱ በነበረው ከፍተኛ መብረቅ ምክንያት ለተወሰኑ ሰዐታት ለመዘግየት ተገዶ ነበርም ተብሏል።

ሲቲ በውድድር ዘመኑ የፕሪሚየር ሊጉን ፣ ኤፍኤካፕ እና ሻምፒየንስ ሊግ ክብሮችን በማሳካት በዚህ በኩል በከተማ ተቀናቃኙ ለሀያ አራት አመታት የተያዘውን ሪከርድ መጋራት መቻሉ ይታወቃል።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
510 viewsYishak Belay, edited  03:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-13 06:19:06
ፓሪስ ሴንት ዠርመን ምባፔን ለመሸጥ ተዘጋጅቷል

ፓሪስ ሴንት ዠርመን ፈረንሳዊው አጥቂው ክልያን ምባፔን በቀጣይ የውድድር ዘመን መጨረሻ በነጻ ዝውውር ላለማጣት በማሰብ በክረምቱ የዝውውር መስኮት ሊሸጠው እንደተዘጋጀ ይፋ ተደርጓል።

የ24 አመቱ አጥቂ በላፓሪዚያኖቹ ቤት ያለው የኮንትራት ውል ቆይታ በቀጣይ የውድድር አመት መጨረሻ የሚጠናቀቅ ይሆናል።

ተጫዋቹ ላለፉት ወራት በውል እድሳቱ ዙሪያ ሲነጋገር ከቆየ በኋላ በዋና ከተማው ለተጫማሪ አመታት የመቆየት ፍላጎት እንደሌለው አስታውቋል ተብሏል።

የፒኤስጂ የምንግዜውም ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪ በስፔኑ ታላቅ ክለብ ሪያል ማድሪድ በጥብቅ የሚፈለግ ተጫዋች መሆኑ የሚታወቅ ነው።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
494 viewsYishak Belay, edited  03:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 19:23:24
ሲልቪዬ ቤርሎስኮኒ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ

የቀድሞ የኤሲ ሚላን እና የአሁኑ ሞንዛ እግር ኳስ ክለብ ፕሬዝዳንት ሲልቪዬ ቤርሎስኮኒ ከደም ካንሰር ጋር ሲታገሉ ቆይተው ዛሬ ማለዳ ላይ በ86 አመታቸው  ህይወታቸው ማለፉ ይፋ ተደርጓል።

ጣልያናዊው ከ31 አመታት የሳንሴሮው ክለብ ባለቤትነት   በ2017 ከተለያዩ ከ18 ወራት በኋላ ሞንዛን መረከባቸው የሚታወስ ነው።

የቀድሞ የሚላን ተጫዋች እና አሰልጣኝ ካርሎ አንቼሎቲ ሀዘናቸውን ከገለጹ  ግለሰቦች እና ክለቦች መካከልም ግንባሩ ቀደሙ ናቸው።

ኤሲ ሚላን እግር ኳስ ክለብ በተመሳሳይ በቀድሞ ባለቤቱ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን አስታውቋል።

ቢሊየነሩ የቢዝነስ ሰው ወደ ፖለቲካው አለም ከመግባታቸው በፊት በጣልያን ግዙፍ የሚዲያ ኩባንያ እንደነበራቸው የሚታወቅ ነው።

ከ1986-2017 ኤሲ ሚላን በባለቤትነት የመሩት ቤርሎስኮኒ በ627.5 ሚሊየን ፓወንድ በ2017 የክለቡን ከፍተኛ ድርሻቸውን መሸጣቸው ይታወሳል።

በቆይታቸው አምስት የሻምፒየንስ ሊግ ፣ ስምንት የሴሪአ እና አንድ የኮፓ ኢታሊያን ማሳካት ችለዋል።

በተጫማሪም አምስት የሱፐር ካፕ ፣ አምስት የኢንተር ኮንትኔንታል እና  አንድ የአለም ክለቦች ዋንጫን አሳክተዋል።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
670 viewsYishak Belay, edited  16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 19:19:40
ሰርቢያዊው ኮከብ ኖቫክ ጆኮቪች የፍሬንች ኦፕን ሮላንድ ጋሮስ ውድድር አሸናፊ ሆኗል

የ36 አመቱ ጆኮቪች በፍጻሜው ተፋላሚው የነበረውን ካስፐር ሩድ በመርታት ሪከርድ የሆነው 23ኛ የግራንድ ስላሙን አሳክቷል።

ሰርቢያዊው በ2008 የመጀመሪያ ግራንድ ስላሙን የአውስትራሊያ ኦፕንን በማሽነፍ ማሳካቱ የሚታወስ ነው።

በሴቶቹ ፖላንዳዊቷ የአለም ቁጥር አንድ ኢቫ ሲቪያቴክ በፍጻሜው ተፋላሚዋ የነበረችውን ካሮሊና ሙቾቫን በመርታት በአራት አመታት ጊዜ ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ የፍሬንች ኦፕን አሸናፊ መሆኗን አረጋግጣለች።

Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
614 viewsYishak Belay, edited  16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 19:15:07
ደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ኡራጓይ የአለም  ከ20 አመት በታች እግር ኳስ ዋንጫ አሸናፊ  ሆናለች

በአርጀንቲና አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየዉ የ2023 ከ20 አመት በታች የአለም እግር ኳስ  ዋንጫ ዉድድር  ሲጠናቀቅ ኡራጓይ ጣሊያንን 1ለ0 በመርታት በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ከ20 አመት በታች የአለም እግር ኳስ  ዋንጫ አሸናፊ መሆን ችላለች።

ሉቺያኖ ሮድሪጌዝ በ86ኛው ደቂቃ በግንባሩ በመግጨት ያስቆጠራት  ብቸኛ  ጎል ኡራጓይን ሻምፒዮን ስታደርግ በውድድሩ የአውሮፓ ቡድኖችን ለአራት ተከታታይ ጊዜ ሻምፒዮን የሆኑበትን ጉዞ ያስቆመችም ሆናለች።

በዲዬጎ አርማንዶ ማራዶና ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ከ40,000 በላይ ተመልካቾች የታደሙ ሲሆን የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖም ተገኝተዋል።

ኡራጓይ በ1997 እና 2013 በዉድድሩ ለፍፃሜ ደርሳ ዋንጫዉን ማጣቷ የሚታወስ ነዉ።

ብራዚል በ2011 ከደቡብ አሜሪካ የመጨረሻው የዉድድሩ አሸናፊ የነበረች ሀገር ናት።

ከዚህ ጨዋታ ቀደም ብሎ በዉድድሩ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈችዉ እስራኤል ደቡብ ኮሪያን 3ለ1 በማሸነፍ ሶስተኛ ደረጃን ማግኘት ችላለች።

Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
566 viewsYishak Belay, edited  16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 16:33:50
ጁልያ ሮበርትስ የእንኳን ደስ አለህ መልዕክት እንዳስተላለችለት ተገልጿል

ፔፕ ጋርዲዮላ ከማንቺስተር ሲቲ ጋር የሻምፒየንስ ሊጉን ዋንጫ በማንሳት የውድድር ዘመኑን በሶስትዮሽ ዋንጫ ክብር ካጠናቀቀ በኋላ ተምሳሌቴ ከሚላቸው እና ከሚያደንቃቸው ሶስት ግለሰቦች መካከል አንዷ የሆነችው የሆሊውድ ፈርጥ የሴት ተዋናይዋ ጁልያ ሮበርትስ የእንኳን ደስ አለህ መልዕክት እንዳስተላለችለት ተገልጿል።

የሲቲ እግር ኳስ ክለብ አሜሪካዊቷ ተዋናይ በኢንስታግራም ገጻቸው የእንኳን ደስ አለህ መልዕክት ጽሁፏን እንዳሳፈረች  አስታውቋል።

ፔፕ በመጋቢት ወር ቡድኑ በሻምፒየንስ ሊጉ ጥሎ ማለፍ አስራ ስድስት የመልስ  ጨዋታ በኢትሀድ አርብ ሌይፕዚግን ሰባት ለዜሮ ከረታበት ግጥሚያ በኋላ በህይወቱ ሶስት ተምሳሌቴ የሚላቸው ሰዎች እንዳሉ እና ማይክል ጆርዳን ፣ ታይገር ውድስ እና ጁልያ ሮበርትስ መሆናቸውን ማስታወቁ አይዘነጋም።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
618 viewsYishak Belay, edited  13:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 16:30:04 ሲቲ የ24 ዓመት ታሪክ ተጋርቷል

ማንቺስተር ሲቲ በሻምፒየንስ ሊጉ ፍጻሜ ኢንተር ሚላንን አንድ ለዜሮ በመርታት በውድድር ዘመኑ የሶስትዮሽ ክብርን በማሳካት ማጠናቀቁን ተከትሎ የከተማ ተቀናቃኙ ለ24 አመታት በእንግሊዝ የሶስትዮሽ ዋንጫን በማሳካት ብቸኛው ክለብ ሆኖ የቆየበትን ታሪክ መጋራት ችሏል።

የማንቺስተር ዩናይትድ እና ማንቺስተር ሲቲ የሶስትዮሽ ክብር ውድድር ዘመን ሲነጻጸር

ዩናይትድ የሶስትዮሽ ዋንጫን ባሳካበት የውድድር ዘመን ሽንፈት ያስተናገደው ሶስት ጊዜ ብቻ ነው። በሁሉም ውድድሮች ካደረጋቸው 57 ጨዋታዎች ግን በሚያስገርም መልኩ በ21 አቻ ተለያይቷል።

የሊግ ካፕ ውድድርን ሳያካትት የፔፕ ጋርዲዮላ ቡድን 42 ጨዋታዎችን ሲያሸንፍ 73.7 % የማሸነፍ መቶኛ አለው ።

ዩናይትድ በበኩሉ 33 ሲያሸንፍ 57.9% የማሸነፍ ንጻሬ አለው።

ሲቲ 145 እና ዩናይትድ 121 ጎሎችን ተጋጣሚዎቻቸው መረብ ላይ ሲያሳርፉ ሲቲ በ26 እና ዩናይትድ በ21 ጨዋታዎች መረባቸውን ሳያስደፍሩ ወጥተዋል።

ሲቲ 39 ዩናይትድ ደግሞ 56 ጎሎችን ሲያስተናግዱ ሲቲ በጨዋታ 2.54 ጎሎችን በአማካይ በጨዋታ ሲያስቆጥር  0.68 ደግሞ ጎል በጨዋታ አስተናግዷል።

ዩናይትድ በአንጻሩ 2.12 በአማካይ በጨዋታ ሲያስቆጥር 0.98 ጎል ደግሞ በጨዋታ በአማካይ ጎል  አስተናግዷል።

ሲቲ በጨዋታ አራት እና ከዚያ በላይ ጎል በ16 ጨዋታዎች ላይ ተጋጣሚው መረብ ላይ ሲያሳርፍ  ካደረጋቸው ጨዋታዎች አንጻር ደግሞ 28.1% ይሸፍናል።

በዚህ በኩል ከከተማ ተቀናቃኙም በእጥፍ የሚበልጥ ቁጥር አለው።

አርሊንግ ሀላንድ በውድድር ዘመኑ 51 ጎሎችን በማስቆጠር ለሲቲ የሶስትዮሽ ዋንጫ ክብር ትልቁን ድርሻ ይወስዳል።

በዩናይትድ በኩል በዚህ ደረጃ የጎል ሸክሙን በወቅቱ የወሰደ ተጫዋች አልነበረም።

ድዋይት ዮርክ 29 እና አንዲ ኮል 24 በሁሉም ውድድሮች ለዩናይትድ በማስቆጠር ከፊት የተቀመጡ ተጫዋቾች ነበሩ።

አስደናቂው ኦሊጉናር ሶልሻየር በሊጉ በዘጠኝ ጨዋታዎች ብቻ በቋሚነት  ጀምሮ ዘጠኝ ጎሎችን ሲያስቆጥር  በሁሉም ውድድሮች ደግሞ በአስራ አምስቱ በቋሚነት  ጀምሯል።

በሀያው ደግሞ ከተጠባባቂ ወንበር ተነስቶ ጀምሯል።

በፍጻሜው የሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ ከሼሪንግሀም ጋር በመሆን የሰራው ገድል የማይዘነጋ ነው።

ፖል ስኮልስ እና ሪያን ጊግስ ባለ ሁለት አሀዝ ጎሎችን ከመረብ ማገናኘት የቻሉ ተጫዋቾች ናቸው።


Website : www.hattricksportofficial.com

Website : www.bestsportet.com

Facebook : facebook.com/hattricksportofficial

Facebook : facebook.com/bestsportet

Telegram : t.me/bestsportet

Twitter : twitter.com/bestsportet

#ሀትሪክ_ስፖርት_ኦፊሺያል
ስፖርትን እንመግባለን !!
We Feed Sport...
572 viewsYishak Belay, edited  13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 16:28:22
498 viewsYishak Belay, 13:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ