2022-01-06 12:58:59
#ሜምፊቦስቴ
==========================
ንጉስ ዳዊት እና ሜምፊቦስቴ ፦
2ሳሙ 4፡4, 9፡4-13
ሜምፊቦስቴ የሳኦል የልጅ ልጅ የዮናታን ልጅ ነው፡፡እግሩም ሽባ ነበር
ሽባ የሆነበትም ምክንያት የአያቱን እና የአባቱን ሞት የሰማች ሞግዚት ይዛው ለመሸሽ ስትሞክር ከእጇ በመውደቁ ነው፡፡
2ሳሙ 4፡4
የሜምፊቦስቴ አያት የሆነው ሳኦል የንጉስ ዳዊት ቀንደኛ ጠላት እንደነበር ይታወቃል፡፡
እንዲሁ የሰው ልጆች ምንጭ የሆነው አዳም በሀጥያት ምክንያት የእግዚአብሔር ጠላት ሆነ፡፡ ሮሜ 5፡9
የሜምፊቦስቴ ሞግዚት ይዛው ልትሸሽ ስትሞክር ነው በ 5 አመቱ ወድቆ ሽባ የሆነው፡፡
እንዲሁ የሰው ልጅ በክርስቶስ በማመን በፀጋ ብቻ እንጂ ሞግዚት በሆነው በሙሴ ህግ ህይወት ሊያገኝ እና ከፍርድ ሊያመልጥ አይችልም፡፡
ገላ 2፡16, 3፡17-21,ሉቃ 14፡15
የሜምፊቦስቴ አባት ዮናታን የንጉስ ዳዊት የልብ ጓደኛ ከመሆኑ የተነሳ ንጉሱ ስለ ዮናታን ቸርነት እና ምህረት ማድረግ ፈለገ፡፡
2ሳሙ 9፡7
እግዚአብሔር ለሀጢያተኛው ሰው በክርስቶስ በኩል ምህረት ማድረግ እና ከቁጣው ሊያድነው ፈለገ።
ዮሐ 3፡14-18,ሮሜ 3፡21,ሮሜ 4፡22- ,5:1, ኤፌ 2፡4-6
ሜምፊቦስቴ ይኖር የነበረው ሎዶባር (ምድረበዳ) በሚባል ቦታ ነበር፡፡ 2ሳሙ 9፡4
የሰው ልጅም በሀጥያቱ ምክንያት ከእግዚአብሔር መገኝት እና መግቦት ርቆ ይኖር ነበር፡፡ ኤፌ 2፡11, 1ጴጥ 2፡25
ሜምፊቦስቴ ካለበት ቦታ ወደ ንጉስ ወደ ዳዊት እንዳይሄድ እግሩ ሽባ ነው ንጉስ ዳዊት ግን መልዕክተኛ በመላክ ወደ እርሱ እንዲመጣ አደረገው፡፡ 2ሳሙ 9፡1-2
ሀጥያተኛ የሆነውም የሰው ልጅ በራሱ መልካም ስራ ወደ እግዚአብሔር መሄድና በአምላክ ፊት ተቀባይነት ማግኘት ስለማይችል እግዚአብሔር ግን በክርስቶስ ወደ ራሱ ማቅረብ ፈለገ፡፡ ኤፌ2፡8, 18, ሮሜ 3፡21-24,ሮሜ 5፡6-10,
ንጉስ ዳዊት ስለ ዮናታን ሲል ለሜምፊቦስቴ ቸርነትን አደረገለት ሜምፊቦስቴም ከዚያን ጊዜ ጀምሮ
2ሳሙ 9፡7
1) እንደ ንጉስ ልጅ ሆነ
2) ከንጉሱ ጋ በማእድ ተቀምጦ ንጉሱ የሚበላውን በላ
3) በኢየሩሳሌም ከንጉሱ ጋር መኖር ጀመረ
4) የአያቱን ምድራዊ ርስት መለሰለት
እንዲሁ እግዚአብሔር በክርስቶስ የቤዛነት ስራ ያመነውን ሀጥያተኛ ሰው በክርስቶስ ምክንያት
1) ልጅ አደረገው
2) በክብር በክርስቶስ በቀኙ አስቀመጠን
3) የሕይወት እንጀራ የሆነው ክርስቶስ ምግቡ ሆነለት
4) በአዲሲቱ ኢየሩሳሌም በክርስቶስ መኖር ጀመረ
5) በአዳም ምክንያት ካጣነው በላይ በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ ባረከን ፡፡ ኤፌ 1፡3, ዮሐ 1፡12,1ዮሐ 3፡1-,ዮሐ 6
ኤፌ 2:6-7,ዕብ12:22-24
ቅዱሳን ልብ ሊሉት የሚገባ፦
===========================
ሜምፊቦስቴ በንጉስ ዳዊት ቸርነት እንዲህ ቢሆንም አሁንም ግን #እግሩ #ሽባ #ነው፡፡
ሰው በክርስቶስ አምኖ ከዳነ በኃላ ለመኖር መፍጨርጨር የለበትም ይልቅስ ጻዲቅ በእምነት በሕይወት ይኖራል፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር ወደ ሕይወቱ የጠራን እንድንኖርለት ሳይሆን ክርስቶስ በእኛ እንዲኖር ነው።
ገላትያ 2 (Galatians)
20፤ ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።
ፀጋ እና ሰላም ይብዛላችሁ።
የወንጌል እውነት አገልግሎት ጅማ
1.4K views09:58