Get Mystery Box with random crypto!

ዝክረ ብሒለ አበው

የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የቴሌግራም ቻናል አርማ behileabew — ዝክረ ብሒለ አበው
የሰርጥ አድራሻ: @behileabew
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 345

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-01-22 19:07:49 #ጥር_15_ዕረፍቱ_ለቅዱስ_ቂርቆስ።

ቅዱስ ቂርቆስ ከእናቱ ከቅድስት ኢየሉጣ ፤ ከአባቱ ከቆዝሞስ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግሥት ነበር ነበር የተወለደው፡፡ ዲዮቅልጥያኖስ 303 ዓ.ም አካባቢ የጣዖት ቤቶች እንዱከፈቱ ቤተ ክርስቲያናት እንዱዘጉ አደረገ ፤ ይህ የዲዮቅልጥያኖስ ዘመነ መንግሥት የክብር ባለቤት የሆነው ክርስቶስን በሚያምኑ ክርስቲያኖች ላይ ታላቅ መከራና ስደት የሆነበት ወቅት ነበር፡፡ በዚያም ሀገር ስሟ ኢየሉጣ የምትባል አንዱት ሴት ነበረች፡፡ ከታናሽነቷ ጀምራ ደግ ለደሀ ለተቸገረ የምትራራ ምስኪን ሴት ነበረች፡፡

በዚህም ሀገር በክርስቲያኖች ላይ ስደት እንደሆነ በሰማች ጊዜ መኮንኑን ከመፍራት የተነሳ ሕፃኗን ይዚ ከሮም ከተማ ተሰዳ ኪልቅያ አውራጃ ከሆነ ከጠርሴስ ደርሳ በዚያም በተለያዩ ሀገሮች ውስጥ እየተዘዋወረች ተቀመጠች፡፡በዚህ በጠርሴስ ተቀምጣ ሳለች ያ ከሮም እርሱን ፈርታ ሸሽታው የመጣችው መኮንን ወደ ጠርሴስ እንደገባ ሰማች፡፡ ይህ መኮንን ወደ ጠርሴስ የመጣው ከሮም የእርሱን ትዕዚዜ እምቢ ብለው ሸሽተው የመጡትን ክርስቲያኖች ፍለጋ ነበር፡፡ ኢየሉጣም ይህን በመስማቷ እጅግ በጣም ተረብሻ ቤቷን ዘግታ በፍርሃት ተውጣ ተቀምጣለች፡፡ የመኮንኑ ጭፍሮች ክርስቲያኖችን ፍለጋ በጠርሴስ አሰሳ ጀምረዋል፡፡ ኢየሉጣ በዚያ ቤት ውስጥ በፍርሃት ተቀምጣ ሳለ በሩ በድንገት ተንኳኳ፡፡

ኢየሉጣ ግን ተነሥታ ለመክፈት አልደፈረችም፡፡ ሉያንኳኩ የነበሩት ሰዎች በሩን በርግደው ገቡ፡፡ የእለእስክንድሮስ ጭፍሮች ነበሩ፤ ‹‹ተነሽ….ውጪ…..›› አለ አንደኛው ወታደር ፤ ከዙያም ይዘዋት እያንገላቱ ወደ መኮንኑ ወሰደዋት ፤ ለመኮንኑም የክርስቲያን ወገን እንደሆነች ነገሩት፡፡

መኮንኑም ‹‹ሴትዮ ተናገሪ ከወዳት ሕዜብ ነው የመጣሽው?….. ነገድሽስ ምንድን ነው? ሀገርሽስ ወዳት ነው?›› አላት፡፡ ኢየሉጣም ‹‹የአንጌቤን ሰው ነኝ ወገኖቼም ኤሳውሮሳውያን ናቸው፤እኔም በአንተ ምክንያት ሸሽቼ ነበር የወደዙህ የመጣሁት አነሆ ዚሬ ግን በእጅህ ውስጥ ነኝ›› አለችው፡፡ መኮንኑም ጏርነን ባለድምፅ ‹‹በእጄ ውስጥ እንደተገኘሽ ታውቂያለሽ አሁንም የማሸልሽን ምረሙ ስምሽን ተናጋሪ እኔንም እሺ በይኝና ለአማልክት ሠዊ›› አላት፡፡

‹‹ለረከሱ አማልዕክት እኔ አልሠማውም›› ብላ በድፍረት ተናገረች፡፡ ‹‹ለመሆኑ ስመሽ ማን ነው?›› ሲል መኮንኑ ጠየቃት ፤ እርሷም ‹‹የእኔ ስም ክርስቲያን መባል ነው›› አለችው፡፡ መኮንኑም መልሶ ‹‹ይህ ስንፍና ነው አይጠቅምሽም እንዳትሞቺ ስምሽን ተናገሪ›› አላት፡፡ የከበረች ኢየሉጣም ‹‹የኔ ስም ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞት የሚሽረው በሰዎች ዘንድ የምጠራበትን ከፈለግህ ስሜ ኢየሉጣ ነው›› ብላ መለሰችለት፡፡ መኮንኑም የቅድስት ኢየሉጣ አመላለስ በጣም አሰባጭቶት ‹‹ፅኑ የሆኑ ስቃዮችን በላይሽ ሳያመጡ ተነሥትሽ መሥዋዕትን ለአማልክት አቅርቢ›› አላት፡፡

ኢየሉጣም ‹‹እውነትን ለመሥራት የምትፈልግ ከሆነ የሦስት ዓመት ልጅ አለኝ እርሱን ፈልገው ያመጡ ዘንድ ጭፈሮችህን ላክ›› አለቸው፡፡ ያን ጊዜም መኮንት የሦስት ዓመት ልጅ ይፈልጉ ዘንድ ወታደሮችን ላከ የሀገር ሰዎችም ልጆቻቸውን ወታደሮች እንዳይገደለባቸው በመፍራት ደብቀዋልና አንዳችም ሕፃን አላገኙም፡፡ ከከተማው ቅጽር በፀሐይ መውጫ ወዳለው በረሃ ወጡ፤የቅድስት ኢየሉጣ ልጅ የሆነውን አንድ ሕፃን ልጅ አገኙት፡፡ አብረውት የነበሩትንም ሰዎች ‹‹የስንት ዓመት ልጅ ነው›› ብለው ጠየቁቸው፡፡ ሰዎቹም ‹‹ይህ ሕፃን የሦስት ዓመት ልጅ ሲሆን ባሏ የሞተባት የክርስቲያናዊት ሴት ልጅ ነው›› አላቸው፡፡

ያንንም ሕፃን ይዘው ወደ መኯንኑ ወሰደት፡፡ መልኩ የሚያምርና ደም ግባት ያለው እንደሆነ መኮንኑም በአየው ጊዜ ‹‹ደስ የምትል አንተ ደስተኛ ሕፃን ሰላምታ ይገባሃል›› አለው፡፡ ‹‹ሕፃኑ እኔን ደስተኛ በማለትህ መልካም ተናገርክ አንተ ግን ደስታ የለህም እግዙአብሔር ለሚዘነጉ ለማይሰሙት ለማይቀበለት ደስታ የላቸውም›› ብል መለሰለት፡፡ መኮንኑም ሕፃኑን ‹‹ሳልጠይቅህ ይህንን ያህል ትመልስልኛለህን?›› አለው፡፡ ሕፃኑም ‹‹ገና ምን አይተህ ከዙህ የበዚ ነገር እመልስልሀለሁ›› አለው፡፡‹‹ስምህ ማነው?›› ሲል መኮንኑ ሕፃኑን ጠየቀው ‹‹ከንጹሕ አዘቅት እና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ሕፃን ስሜ ክርስቲያን መባል ነው›› ብል መለሰለት፡፡ መኮንኑም የእናትና የሕፃኑ መልስ አንድ መሆኑ በአንድ በኩል ገርሞታል በላላ በኩል ደግሞ አበሳጭቶታል፡፡ መኮንኑም በመቆጣት ‹‹ዳግመኛ እንዳትሞት ስምህን ንገረኝ አለው›› ቅስ ቂርቆስም ‹‹የከበረ ሕፃን ስሜ ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ መጠሪያ ስሜን የምትሻ ከሆነ እናቴ የሰየመችልኝ ስሜ ቂርቆስ የሚለው ነው›› አለው መኮንኑ ሕፃኑን ዜግ ባለ ድምጽ ‹‹እሺ በለኝ ለአማልክትም ሠዋ በስጋህ ስታድግ እሾምሀለሁ በብዙ ወርቅና ብርም አከብርሀለሁ›› ብል በተማጽኖ ቃል ሕፃኑን ሉያታል ጀመረ ፤ ሕፃኑም ‹‹የሰይጣን መልእክተኛ ለእውነትም ጠሎቷ የሆንክ ከኔ ራቅ›› አለው፡፡ መኮንኑም የልጁን ድፍረት ሰምቶ በጣም ተቆጣ ወታደሮቹንም ጠርቶ ሕፃኑን ወስደው እንዱያሠቃዩትና ያ ሲነኩት እንኳን እንደጥጥ የሚለሰልሱ ቆዳዎቹን ደሙ እንደ ውኃ እስከሚፈስ አስገረፈው ፤ የከበረች ኢየሉጣም የልጇን ትዕግሥት ባየች ጊዜ እግዙብሔርን አመሰገነች፡፡

እለእስክንድሮስ በተለያዩ ዓለማዊ ሀብት ለማታለል ቢሞክርም አለተሳካለትም ፤ የተለያየ ስቃይ እያደረሰባቸው እንኳን ለጣዖት አንሰግድም ስላለት ፤ በብረት ጋን ውስጥ ውኃ አፍልተው እንዱጥሏቸው አዘዘ፡፡ ጭፍሮቹም በትልቅ ጋን ውስጥ ውኃ አፍልተው አዘጋጁ ፤ የውኃው ፍላት እንደ ክረምት ነጎድጓድ በርኅቀት ላለ ሰዎች ሳይቀር ይሰማ ነበረ፡፡ ወታደሮቹም ሉከቷቸው ሲወስዶቸው ኢየሉጣ ልቧ በፍርሃት ታወከ ፤ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ፍርሃቷ ይርቅላት ዘንድ ወደ እግዙአብሔር ይጸልይላት ነበረ ፤ እናቱንም ‹‹ሁለተኛ ሞት በሰማይ አያገኝንምና እናቴ ሆይ በርቺ ጨክኚ ፤ አናንያ አዚርያ ሚሳኤልን ያዳነ እኛንም ያድነናል›› አላት፡፡ ከዙህ በኋላ እሷም ጨክና በፍጹም ልቡ ሆነው ተያይዘው ወደ ፈላው ውኃ ገቡ ፤ ያን ጊዜ በማያምኑ ሰዎች ፊት በጽናት የመሠከሩለት የዓለሙ መድኃኒት ልዑል እግዙአብሔር ሐምሌ 19 ቀን አገልጋዩን የራማውን ልዑል ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ በበትረ መስቀለ እሳቱን አጥፍቶ የፈላውንና ውኃ አቀዜቅዝ አውጥቷቸዋል፡፡ ከውኃው በወጡም ጊዜ ልብሳቸው ሳይበሰብስ ሰውነታቸው ሳይሸበሸብ ታዩ ፤ በዚህም ምክንያት ከአሕዚብ (ከማያምኑ ሰዎች) ብዙዎች አምነው አንገታቸውን ለሠይፍ ፤ አካላቸውን ለእሳት ሰጥተዋል፡፡

መኮንኑም በታላቅ ስቃይ ያሰቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው። በዚህን ጊዜ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስን አረጋጋው አጽናናው ስሙን ጠርተው መታሰቢያ ለሚያደርጉለትም በረከትን እንደሚያገኝና ሌላ ብዙ ቃል ኪዳን ሰጠው። ሲነጋ መኮንኑ ከመካነ ምኩናኑ ተቀምጦ ካለበት አስጠርቶ “የተመለስከው መመለስ አለን?” አለው:: ቅዱስ ቂርቆስም “አይሆንም አልመለስም” አለው:: ሰይፍ ጃግሬውን ጠርቶ “ንሳ ውደቅበት” አለው:: በሰይፍ መታው: ጌታም ነፍሱን ከመካነ ዕረፍት ሥጋውንም ነጥቆ በሰረገላ ኤልያስ አኑሮለታል:: እናቱ ቅድስት ኢየሉጣንም በማግስቱ (ጥር 16) በሰይፍ አስመትቷት በሰማዕትነት ዓርፋለች::
80 viewsbisrat, 16:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-21 11:35:34
84 viewsbisrat, 08:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-21 11:34:13 #ጥር_14_ታላቁ_መናኝ_አቡነ_አረጋዊ_የተወለዱበት_ዕለት_ነው።

ከዘጠኙ ቅዱሳን አባቶች አንዱ የሆኑት አቡነ አረጋዊ ከአባታቸው ንጉሥ ይስሐቅ እና ከእናታቸው ንግሥት አድና በሮም ሀገር ጥር 14 ቀን ተወለዱ፡፡ የመጀመሪያ ስማቸው ዘሚካኤል ይባላል፡፡ በዘመኑ የነበረውን መንፈሳዊ ትምህርት እየተማሩ አደጒ፡፡

 እድሜያቸው አሥራ አራት ዓመት ሲሞላ ቤተሰቦቻቸው ከነገሥታት ቤተሰብ ሚስት አጩላቸው፡፡  ነገር ግን አቡነ አረጋዊ ይህን ሲሰሙ ከነበራቸው የክርስቶስ ፍቅር የተነሳ ትዳር መመሥረትን ትተው ደውናስ ወደ ምትባል ገዳም ሔዱ፤ በዚያም አባ ጳኩሚስ ይኖሩ ነበር።

አበምኔቱ አባ ጳኩሚስን ልበሰ ምንኩስናን እንዲያለብሳቸው ጠየቁት። አባ ጳኩሚስም ‹ልጄ ሆይ አንተ የንጉሥ ልጅ እንደ መሆንህ መጠን የመንግሥቱ ወራሽ ነህና መንኩሰህ ለመኖር ይቻልሃልን?› አለው፡፡ ቅዱስ አባታችንም ‹‹አባቴ ሆይ የምድር መንግሥት ኃላፊ ጠፊ ነው፤ ነገር ግን የማታልፈውንና የማትጠፋውን ዘለዓለማዊት መንግሥት እወርስ ዘንድ እፈልጋለሁ›› አለው፡፡ እናም በ14 ዓመታቸው በአባ ጳኩሚስ እጅ የምንኩስናውን ልብስ ለበሱ፤ በገዳሙም እየተጉ ኖሩ፡፡

 አቡነ አረጋዊ እጅግ በጣም መንፈሳዊ ሰው ነበሩ፡፡ በሕይወታቸው እና ለመንፈሳዊ ሕይወት በነበራቸው መንፈሳዊ ቅንዓት
ብዙዎችን ወደ እግዚአብሔር መልሰዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ስማቸው አቡነ አረጋዊ ተባለ አረጋዊ ማለት ብልህ (አዋቂ) ማለት ነው፡፡

ከዚህ በኋላ የጻድቁ ዜና በሀገራቸው ሮም ውስጥ እንዲሁም በመላው ቦታ ተሰማ፡፡ በዚህም የተማረኩት ሰባት ቅዱሳን፤
-አባ ሊቃኖስ ከቁስጥንጥንያ፣
-አባ ይምአታ ከቆስያ፣
-አባ ጽሕማ ከአንጾኪያ፣
-አባ ጉባ ከቂልቅያ፣
-አባ አፍፄ ከእስያ፣
-አባ ጰንጠሌዎን ከሮም፣
-አባ አሌፍ ከቂሳርያ እርሱ ወዳለበት ገዳም መጡ። አባ ጳኩሚስ ለብዙ ዓመታት ምንኩስናን ሥርዓተ ማኅበርን አስተማራቸው።

 ከዚህ በኋላ እናታቸው ንግሥት አድና ዜናቸውን ሰምታ አቡነ አረጋዊን ልትይጠይቃቸው ወደ አሉበት መጣች፡፡ ‹‹እናቴ ስለምን መጣሽ?›› ሲሉ ጠየቋት፡፡ እናታቸውም እርሳቸው የናቁትን ዓለም ንቃ እንደመጣች ነገረቻቸው፡፡

አቡነ አረጋዊ በእናታቸው ውሳኔ በጣም ተደስተው፤ እናታቸው የምንኲስና ማእረግ እንዲቀበሉ እና በሴቶች ገዳም እንዲኖሩ አደረጒአቸው፡፡

ከሰባት ዓመት በኋላ ወደ ሮም ተመልሰው ሲያስተምሩ የሀገራችንን የኢትዮጵያን ዜና ሰምተው አባታችን ዘሚካኤል (አቡነ አረጋዊ) ከስምንቱ ቅዱሳን ጋር በመሆን በአልዓሜዳ አምስተኛ የንግሥና ዓመት በ480 ዓ.ም ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡

በኋላም ንጉሥ አልዓሜዳ ከሞተ በኋላ በነገሠው በታዜና ስድስተኛ የንግሥና ዓመት ላይ  ‹‹ተለያይተን እናስተምር›› ብለው ወስነው ተለያዩ።
-አቡነ ሊቃኖስ ደብረ ቆናጽል፣
-አባ ጰንጠሌዎን ከእዚሁ ሁለት ምዕራፍ እልፍ ብሎ ከሚገኝ ኮረብታ፣
-አቡነ ይስሐቅ መደራ፣
-አቡነ ጉባ በእዚሁ በመደራ ትይዩ ሦስት ምዕራፍ እልፍ ብሎ፣
-አባ ጽሕማ፣ አባ ይምዓታ ገርዓልታ፣
-አባ አሌፍ አሕስዓ ብሕዛ በተባለችው፣
-አባ አፍጼ ይሐ ተሠማሩ።

አቡነ አረጋዊም እናታቸውንና ማትያስ የተባለ ደቀ መዝሙራቸውን ይዘው በብዙ ቦታዎች እያስተማሩና ሕሙማንን እየፈወሱ ደብረ ዳሞ የሚባል ስፍራ ደረሱ፡፡ ነገር ግን መውጫ የሌለው ረዥም ተራራ ስለነበር “አሁን ይህን ተራራ በምን ልወጣው እችላለሁ?” እያሉ ሲጨነቁ እግዚአብሔር ዘንዶ ተሸክሞ እንዲያወጣቸው አደረገ፡፡

ከዚህ በኋላ እግዚአብሔርን እያገለገሉ በጸሎትና በጾም ኖሩ፡፡ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦላቸው፤ ሰማያዊ መንግሥትን እንደሚያወርሳቸው፣ በእርሳቸው አማላጅነት ለሚታመኑም የእርሳቸውን ጸጋ እና በረከት እንደሚያገኙ ቃል ገባላቸው፡፡

አቡነ አረጋዊ ደቀ መዝሙሮቻቸውን ሰብስበው ‹‹ከእንግዲህ በሥጋ አታዩኝም›› ብለው ነግረዋቸው ጥቅምት 14 በ99 ዓመታቸው ተሰወሩ፡፡

#እግዚአብሔር_በጸሎታቸው_ይማረን!!!
80 viewsbisrat, 08:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-19 18:17:35
80 viewsbisrat, 15:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-19 18:15:30 መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ብሏታል እርሷን ከያዝን እግዚአብሔርን እንይዘዋለን፤ ያለእርሷ እንሥራችን አይሞላም ለዘመናት ደክመናል ነገር ግን እንስራችን ባዶ ነው፡፡ “እመቤቴ ከቤቴ ግቢ፤ ቤቴ ባዶ ነው” እንበላት፤ ትመጣለች ያን ጊዜ ቤታችን ይሞላል፡፡ የፍቅር ወይን፤ የቸርነት ወይን፤ የሰላም ወይን፤ የመተማመን ወይን በቤታችን ጎድሎብናል፡፡ ስለዚህ

እመቤታችን በምልጃዋ ትሙላልን፤ ፍቅሯን ታሳድርብን፡፡ አሜን፡፡
75 viewsbisrat, 15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-19 18:15:30 #ጥር_12_ጌታችን_የፈጸመው_የመጀመሪያው_ተአምሩ_የሚታሰብበት_በዓል_ነው።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላ አውራጃ በዳዊት ከተማ በቤተልሔም ምድረ ኤፍራታ ተወልዶ በሠላሣ ዘመኑ በሠላሣ ዓመተ ምሕረት በፈለገ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ተጠምቆ ሳይውል ሳያድር ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ጾመ ጸለየ፤ በጠላት ዲያብሎስ ተፈተነ። ፈተናውን ድል አድርጎ ሱባኤውን ፈጽሞ በወጣ በሦስተኛው ቀን ከእናቱ ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም እና ከቅዱሳን ሐዋርያቱ ጋር በመሆን በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር በሰርግ ቤት ተገኝቶ ቤተ ከብካቡን በትምህርቱ በተአምራቱ ባረከ። ኢየሱስ ክርስቶስ ይኽን ድንቅ ተአምር በቃና ዘገሊላ ያደረገው በገዳመ ቆሮንቶስ ሱባኤውን ፈጽሞ በወጣ በሦስተኛው ቀን የካቲት 23 ቀን ነው። ይሁንና አባቶቻችን ሊቃውንት «የውኃ በዓል ከውኃ በዓል ጋር መቀናጀት አለበት» በማለት በጥምቀት በዓል ማግስት ጥር 12 ቀን እንዲከበር አድርገውታል። እኛም ይኽንኑ ቀን ጠብቀን በዓሉን በማክበር ላይ እንገኛለን።

 የዮሐንስ ወንጌል ም.2፤1 “በሦስተኛው ቀን በገሊላ አውራጃ በቃና ሰርግ ነበር” ይላል፡፡ ከዚህ በኋላ የታሪኩን ምስጢራዊ ትርጉም በቅደም ተከተል እንመልከት:-

1.“#የኢየሱስ_እናት_በዚያ_ነበረች_ኢየሱስ_ደቀመዛሙርቱ” ይላል፡፡ከዚህ ላይ የምንረዳው መጀመሪያ እመቤታችን ድንግል ማርያም አስቀድማ በሰርጉ ውስጥ መኖሯን ነው፡፡ እናት ከተጠራ በኋላ ነው ልጅ የሚጠራና ከዚያም ኢየሱስ ክርስቶስ፤ ከመምህር ጋር ደቀመዝሙር ይጠራልና ከእርሱም ጋር ደቀመዛሙርቱ ተጠሩ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር በወቅቱ ወይን ባለቀ ጊዜ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወይን የላቸውም ያለችው፡፡ እርሱም “ከአንቺ ጋር ምን አለኝ፤ ጊዜዬ ገና አልደረሰምና” አላት፡፡ ወደምሥጢሩ ስንገባ፤

2.#ሦስተኛ_ቀን_ምንድን_ነው?
#ሀ. ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀ ጥር 11 ቀን ነው፡፡ ወዲያውኑ እንደተጠመቀ ሳይውል ገዳመ ቆሮንቶስ ሄደ፤ 40 ቀንና 40 ሌሊት ጾመ፤ ጾሙ የካቲት 20 ቀን ይፈጸምና የካቲት 23 ቀን “በሦስተኛው ቀን ሰርግ ነበር” ይላል፡፡

#ለ_ሦስተኛ_ቀን_የሚለው · የመጀመሪያ ቀን የሚባለው ዘመነ አበው ፤ አዳም፤ እነአብርሃም፤ ይስሐቅ አበው የነበሩበት ዘመን ሲሆን፤ · ሁለተኛ ቀን የሚባለው ዘመነ ኦሪት ነው፤ እነሙሴ የነበሩበት ዘመን ሲሆን · ሦስተኛ ቀን የተባለው ዘመነ ሐዲስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነበት ዘመን ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር ሰርግ የሆነው፡፡

3.“#እመቤታችን_አስቀድማ_ነበር” ሲል ደግሞ እመቤታችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በሥጋዊ እድገቱ እንደምትቀድመው ነው፡፡ እንኳን የእርሱ እናት ትቅርና ዮሐንስ መጥምቁም በ6 ወር ይቀድመው ነበር፡፡ እንግዲህ እናትን ሳያውቁ ልጅን ቢጠይቁ ያስቸግራል፡፡ አስቀድማ የነበረችውን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ከመሆን በፊት አብራን የኖረችውን ድንግል ማርያምን ሳናውቅ ኢየሱስ ብንል ትርፉ ድካም ብቻ እንጂ አይሳካም፡፡ ዛሬም ቢሆን “ኢየሱስ” ከማለት በፊት አስቀድመን እርሷን አማልጅን እንበላት፡፡

ነገረ ድኅነትን ስናስብ በህሊናችን አስቀድመን እርሷን መሳል አለብን፤ ነገረ ማርያም የምሥጢረ ሥጋዌ መቅድም (መጀመሪያ)፤ የነገረ ድኅነት መሠረት ነውና፡፡ ጌታችን ተወለደ፤ ተሰደደ፤ አስተማረ፤ ተሰቀለ፤ ሞተ፤ ተነሳ፤ አረገ፤ ዳግም ይመጣል ሲባል በድንግል ማርያም ሥጋ ነው፡፡ በነገራችን ሁሉ እርሷን ማስቀደም እንዳለብን ነው የምንረዳው፡፡

4.#ወይኑ_ባለቀ_ጊዜ “#ወይን_የላቸውም” አለች፡፡
የወይኑን ማለቅ ለእመቤታችን ማን ነገራት? ሙሽራው ወይስ ከሰርገኞቹ መካከል አንዱ? ለዚህ ምንም አይነት መልስ እንደማይሰጥ ግልጽ ነው፡፡ ድንግል ማርያም ግን እራሷ ነበር ያወቀችው፤ ነቢይት ናትና፡፡ ስለሆነው እንዲሁም ስለሚሆነው ታውቃለች፤

ቅዱስ ዘካርያስና ቅድስት ኤልሳቤጥ ካመሰገኗት በኋላ “ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ይሉኛል” ማለቷ ወደፊት ስለሚመጣው ትውልድ ነበር የተናገረችው፤ ይህ ነቢይነቷን የሚገልጽ ነው፡፡ (ሉቃ. 1፤48-49) ኢሳይያስ በትንቢቱ በምዕራፍ 8፤1 “ወደ ነቢይቱ ሄድኩ ጸንሳም ነበር” የሚላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ነው፡፡

በ2ኛ ነገ. 6፤8 በሶርያ የነበረው ንጉሥ በኢየሩሳሌም ያለውን ንጉሥ ሊወጋ (ሊገድል) በፈለገ ጊዜ በእልፍኝ ሆኖ የሚመክረውን ምክር ነቢዩ ኤልሳዕ ኢየሩሳሌም ሆኖ ይመለከትና ያውቅ ነበር፤ ኢየሩሳሌም ሆኖ በሶርያ የሚደረገውን እያየ ነበር፡፡ ስለዚህም የኢየሩሳሌሙን ንጉሥ “ከቤትህ እንዳትወጣ ሶርያውያን ሊገድሉህ ይፈልጋሉ” እያለ ይመክረው ነበር፡፡ ምን አይነት ጸጋ እንደሆነ አስቡት፤ ኢየሩሳሌም ሆኖ በሶርያ የሚደረገውን ነገር ማወቅ፡፡

ታዲያ በዘመነ ብሉይ የነበሩ ነቢያት እንዲህ የርቀቱን ነገር የሚያውቁ ከሆነ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የዶኪማስን የቤት ችግር፤ የወይን ማለቅ ብታውቅ ብትረዳ ምን ይደንቅ? የመለኮት እናትም እንዴት ጸጋው ይበዛላት? እንደ እመቤታችንስ ጸጋው የበዛለት በዘመነ ብሉይ ማን ነበር? “ጸጋን የተመላሽ ድንግል ሆይ ደስ ይበልሽ” የተባለች ድንግል ማርያም አይደለችምን? እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን፡፡

6. “ #አንቺ_ሴት ”
ጌታችን ይህንን ቃል የተናገረው ሴት የሚል ቃል የፆታ መጠሪያ ነውና በፆታዋ አክብሮ ሲጠራት ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ሔዋን ከአዳም በተፈጠረች ጊዜ አዳም እንዲህ ሲል ተናግሮ ነበር “ይህቺ አጥንት ከአጥንቴ ናት ስጋዋም ከስጋዬ ናት እርሷም ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል” ዘፍ.2፥23 በመሆኑም ጌታችን አንቺ ሴት ማለቱ ከስጋዋ ስጋ ከነፍሳ ነፍስ መንሳቱን ለማጠየቅ ነው ።

6.“#ከአንቺ_ጋር_ምን_አለኝ?” ያላትስ ምን ማለቱ ነበር?
ወግጅልኝ፤ ሂጂልኝ ማለቱ ሳይሆን “ያልሽኝን እንዳልፈጽምልሽ ምን የሚከለክለኝ ነገር አለ” ሲል ነው፡፡ “እናትና አባትህን አክብር፤ ለእናትና ለአባትህ ታዘዝ” ያለ አምላክ እናቱን ሂጂልኝ፤ ወግጅልኝ አላት ሲባል አያሳፍርም? ይህማ እንዳይሆን ለእናቱ እየታዘዘ አደገ ወንጌል ይል የለምን፡፡ (ሉቃ. 2፤51)

7.“#ጊዜዬ_ገና_አልደረሰም”
ይህን ያለው ወይኑ ከእንስራው በደንብ ካለቀ በኋላ ውሀ ሞልተው የጌታን ተአምር እዲታይ ለማድረግ ነው፡፡ ምክንያቱም ወይኑ በደንብ ሳያልቅ ከዚያው ላይ ቢሞላው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ተአምር አይታወቅም፤ ረድኤት አሳደረበት ይባላል አንጂ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወይኑ ሁሉ ካለቀ በኋላ ግን ውሀ ተሞልቶ ወይን ሲሆን ተአምሩ ይታወቃል፤ ይገለጻል፡፡ ለዚህም ነው “ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመጀመሪያውን ተአምር በቃና አደረገ” የሚል፡፡( ሌላም ሰፊ ምሥጢር ቢኖርም ለአሁኑ ግን ይህን አቅርበናል፡፡)

የሰርገኛው ቤት ብቻ አይደለም፤ ወይን የጎደለበት ሁላችንም ወይን የለንም የሕይወት እንሥራችን ጎደሎ ነው፡፡ ይህ እንስራ (ጋን) የሚሞላው በእመብርሀን አማካኝነት ነው፡፡ እርሷ ከሌለችበት በፍጹም ሊሞላ አይችልም በመሆኑም ለሁሉም ሰው ለማስገንዘብ የምንወደው በቅድሚያ ጸጋ የበዛበት እመቤት መያዝ እንዳለብን፤ ለምን እግዚአብሔር ከእርሷ ጋር ነውና፡፡
228 viewsbisrat, 15:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-18 23:36:52 #ጥር_12_ጌታችን_የፈጸመው_የመጀመሪያው_ተአምሩ_የሚታሰብበት_በዓል_ነው።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላ አውራጃ በዳዊት ከተማ በቤተልሔም ምድረ ኤፍራታ ተወልዶ በሠላሣ ዘመኑ በሠላሣ ዓመተ ምሕረት በፈለገ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ተጠምቆ ሳይውል ሳያድር ወደ ገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ጾመ ጸለየ፤ በጠላት ዲያብሎስ ተፈተነ። ፈተናውን ድል አድርጎ ሱባኤውን ፈጽሞ በወጣ በሦስተኛው ቀን ከእናቱ ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም እኘአና ከቅዱሳን ሐዋርያቱ ጋር በመሆን በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር በሰርግ ቤት ተገኝቶ ቤተ ከብካቡን በትምህርቱ በተአምራቱ ባረከ። ኢየሱስ ክርስቶስ ይኽን ድንቅ ተአምር በቃና ዘገሊላ ያደረገው በገዳመ ቆሮንቶስ ሱባኤውን ፈጽሞ በወጣ በሦስተኛው ቀን የካቲት 23 ቀን ነው። ይሁንና አባቶቻችን ሊቃውንት «የውኃ በዓል ከውኃ በዓል ጋር መቀናጀት አለበት» በማለት በጥምቀት በዓል ማግስት ጥር 12 ቀን እንዲከበር አድርገውታል። እኛም ይኽንኑ ቀን ጠብቀን በዓሉን በማክበር ላይ እንገኛለን።

በቃና ዘገሊላ የተደረገው ይኽ ተአምር በዮሐንስ ወንጌል በምእራፍ 2 ከቁጥር 1-11 ድረስ ተጽፎ ይገኛል። በዓሉ ቃና ዘገሊላ የሚል ስያሜ ያገኘውና በዚህ ስም ሊጠራ የቻለው አምላካችን፣ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ሀገር ክፍል በምትሆን ቃና በተባለችው ቦታ በፈጸመው ተአምር ምክንያት መነሻነት ነው። ከቅዱስ መጽሐፍ ላይ ተጽፎ የሚገኘው ሙሉ ቃል እንዲህ ይላል፦ «በሦስተኛውም ቀን በገሊላ ቃና ሰርግ ነበረ፥ የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፤ ኢየሱስም ደግሞ ደቀ መዛሙርቱም ወደ ሰርጉ ታደሙ። የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት። የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም አለችው። ኢየሱስም። አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት። እናቱም ለአገልጋዮቹ። የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ አለቻቸው። አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር። ኢየሱስም። ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው። አሁን ቀድታችሁ ለአሳዳሪው ስጡት አላቸው፤ ሰጡትም። አሳዳሪውም የወይን ጠጅ የሆነውን ውሃ በቀመሰ ጊዜ ከወዴት እንደ መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ። ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል፥ ከሰከሩም በኋላ መናኛውን፤ አንተስ መልካሙን የወይን ጠጅ እስከ አሁን አቆይተሃል አለው። ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።» በቃና ዘገሊላ የተፈጸመው ይኽ ሰርግ ሙሽራ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንድናስብና እንድናስታውስ ያደርገናል። ሚዜው የሙሽራው አገልጋይ ነውና መጥምቁ ዮሐንስ ሙሽራ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ መደሰቱንና ሊያገለግለው የተዘጋጀ መሆኑን ሲያስረዳ ፦ « ሙሽራይቱ ያለችው እርሱ ሙሽራ ነው፤ ቆሞ የሚሰማው ሚዜው ግን በሙሽራው ድምጽ እጅግ ደስ ይለዋል። እንግዲህ ይህ ደስታዬ ተፈጸመ። እርሱ ሊልቅ እኔ ግን ላንስ ያስፈልጋል።» ዮሐ. 3፥29- 30 ይለናል።

በቃና ዘገሊላ በሰርጉ ቤት ተገኝቶ ተአምሩን የጀመረው ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ እና ከሐዋርያት ጋር አብሮ ነበርና አማላጅ እና ተማላጅ ማን እንደሆነ በልዩ ምሥጢር ተስተውሎበታል። ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ በተከታታይ ልዩ የሆነውን ብሥራት ሲያሰማ እንዲህ በማለት ጽፎልናል፦ በስድስተኛው ወር ማለትም መልአኩ ገብርኤል ካህኑ ዘካርያስን «ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥም ወንድ ልጅ ትወልድልሃለች፥ ስሙንም ዮሐንስ ትለዋለህ። ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።» ካለው በኋላ ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በክብር ተገልጦ «ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ።» ብሏታል። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም በአብሣሪው መልአክ በቅዱስ ገብርኤል እንደተነገራት በእውነት ጸጋን የተሞላች ናትና በሰርግ ቤት የጎደለውን የጓዳውን ምሥጢር ተረድታ የሠርጉ ሥነ-ሥርዓት በሠመረና በተዋጣለት ሁኔታ እየተከናወነ ድንገት የወይን ጠጅ በማለቁ ተጨንቀውና ግራ ተጋብተው አስተናባሪዎቹ በታወኩበት ሰዓት የጭንቅ አማላጅ ናትና ወደ ልጅዋ ወደ ወዳጅዋ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘወር ብላ «ወይን እኮ የላቸውም» በማለት አሳስባ ባዶ የሆኑት የድንጋይ ጋኖች ውኃ ተሞልተው ጣፋጭ ወይን ጠጅ ተገኝቶባቸዋል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመልእክቱ « እግዚአብሔርንም የመምሰል ምሥጢር ያለ ጥርጥር ታላቅ ነው፤ በሥጋ የተገለጠ፥ በመንፈስ የጸደቀ፥ ለመላእክት የታየ፥ በአሕዛብ የተሰበከ፥ በዓለም የታመነ፥ በክብር ያረገ። 1ኛጢሞ 3፥16 በማለት እንደጻፈልን ከድንቅ በላይ ድንቅ በሆነ ተዋሕዶ በሥጋ መገለጡ ከእመቤታችን ተወልዶ ነውና በልደቱ ጊዜ አብራ እንደነበረችው እንዲሁ ደግሞ በሞቱ ጊዜ ከእርሱ እንዳልተለየች እንረዳለን። ይኽንንም ወንጌላዊው ዮሐንስ «ነገር ግን በኢየሱስ መስቀል አጠገብ እናቱ፥ የእናቱም እኅት፥ የቀለዮጳም ሚስት ማርያም፥ መግደላዊትም ማርያም ቆመው ነበር።» ዮሐ. 19፥25 በማለት በጻፈልን መልእክት ለማወቅ ችለናል። በመጀመርያ በልደቱ በኋላም በሞቱ ጊዜ አብራው የነበረች ቅድስት ድንግል ማርያም ዘመኗን በሙሉ በፍጹም እንዳልተለየችው ተአምሩን በጀመረበት በቃና ዘገሊላም አብራው ነበረችና ዛሬ ትውልዱ ሁሉ የሚኮራበትን የአማላጅነት ሥራ በቃና ዘገሊላ ፈጽማለች።

«#አንቺ_ሴት_ከአንቺ_ጋር_ምን_አለኝ» በሚለው ቃል ብዙዎች ተሰናክለውበት ቢገኙም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን አምልተውና አስፍተው ምሥጢራትን የነገሯቸው የተዋሕዶ ልጆች ግን በእናትና በልጅ መካከል ያለውን የንግግር ዘይቤ ተረድተው እውነቱን ሲመሰክሩ ይኖራሉ።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ከእግዚአብሔር ተልኮ የመጣውን አብሳሪ መልአክ «እንደ ቃልህ ይደረግልኝ» እንዳለችው ኢየሱስ ክርስቶስም እመቤታችንን «ከአንቺ ጋር ምን አለኝ» (እንደ ቃልሽ ይሁን) በማለት ጥያቄዋን መልሷል፤ ምልጃዋን ተቀብሏል። «ጊዚዬ አልደረሰም» በማለት ቢናገርም ስለ እናቱ ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ሲል የእናቱን ልመና ተቀብሎ ተአምራቱን ፈጽሟል። እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሳይነግሯት በልባቸው ያለውን የምታውቅ እናት ናትና የሰርጉ አስተናባሪዎችን ኃዘን ተመልክታ ከልጇ ከወዳጇ አማልዳ የጎደላቸውን እንደሞላች ለእኛም ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል ብላ በተፈጸመላት ቃል ጎዶሏችንን ትሙላልን። የሰዎችን ጭንቅ አውቃ ሳይነግሯት ያማለደች እናት ስሟን ጠርተው ለሚለምኗትማ የበለጠ ታደርጋለችና ሁላችንንም በተሰጣት ጸጋ ታማልደን።

ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤቷን በረከቷን ያሳድርብን አሜን!!
290 viewsbisrat, 20:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-17 19:27:25 #ሐ_የዕዳ_ደብዳቤያችንን_ይደመስስ_ዘንድ

#3_ጥምቀት_ለምን_በውኃ_ሆነ? ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀው በውኃ ነው እኛም እንድንጠመቅ የታዘዝነው በውኃ ነው ለምን በውኃ ሆነ ጌታችን ጌትነቱን ለመግለጽ ለምን በወተት ፣ በማር አልተጠመቀም? እኛስ ለምን በውኃ እንጠመቃለን፣ በማር በወተት ለምን አለደረገውም ቢሉ በኖኅ ዘመን ፍጥረት ሁሉ በውኃ ጠፍቶ ነበር ከዚህም የተነሣ ውኃ ለመዓት እንደተፈጠረ ይታሰብ ነበር። ዳሩ ግን ውኃ ለምሕረትና ለድኅነት የተፈጠረ መሆኑን ለማሳየት ጌታም ጥምቀቱን በውኃ አድርጓል።

ማርና ወተት በማንኛውም ሰው ቤት አይገኙም ውኃ ግን በሁሉም ቤት ይገኛል። ጥምቀት በማር ወይንም በወተት አንዲሆን ቢደረግ ኖሮ ድኅነት ለሀብታሞች ብቻ በሆነ ነበር። በሁሉም ቤት በሚገኘው ውኃ በማድረጉ ጥምቀት ለሀብታም ለድሀ ሳይባል ለሁሉም እኩሉ እንዲደርስ መደረጉን እንረዳለን። ሌሎች ፈሳሾች አትክልት ላይ ቢያፈሱአቸው አትክልቱን ያደርቃሉ እንጂ አያለመልሙም። ውኃ ግን ያለመልማል እናንተም በውኃ ብትጠመቁ ልምላሜ ሥጋ ልምላሜ ነፍስ ታገኛላችሁ ሲል ነው።

ማርና ወተት ልብስ ቢያጥቡባቸው እድፍ አያጠሩም ውኃ ግን ያጠራል። ከኃጢያት እድፍ በውኃ ተጠምቃችሁ ትጠራላችሁ ለማለት። ውኃ መልክን ያሳያል እናንተም በውኃ ብትጠመቁ የሥላሴን መልክ በመንፈስ ታያላችሁ ሲል ነው። ውኃ እሳትን ያጠፋል እናንተም በውኃ ተጠምቃችሁ የልጅነት ጸጋ ካገኛችሁ ከገሃነም እሳት ትድናላችሁ ሲል ነው። ውኃ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ይደርሳል ጥምቀትም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ተዳርሷል ። ባጠቃላይ የጌታችን መድኃኒታችን ጥምቀት በዓል ከዘጠኙ ዓበይት የጌታችን በዓላት አንዱ ነው። በጥምቀት ልጅነት አግኝተናል።

አንዳንዶች በየዓመቱ የምናከብረው ጥምቀት እና በካህናት የተባረከ ውሃ መረጨታችንን እያዩ በየዓመቱ የምንጠመቅ የሚመስላቸው አሉ። ሆኖም የልጅነት ጥምቀት አንዴ የምትፈፀም ነች። ጥምቀት ከማይደገሙ ምስጢራት ውስጥ ነው። ስለሆነም ወንድ በአርባ፣ ሴት በሰማንያ ቀኖች ወደ ቤተ ክርስቲያን መጥተው ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ አንዴ ልጅነት ያገኛሉ ወይንም እኛ ሁላችን አግኝተናል። በየዓመቱ የምናከብረው የጥምቀት በዓል ጌታችን የሰራልንን አምላካዊ ሥራ የምናደንቅበት እና የምናከብርበት፣ በማክበራችንም የምንባረክባት ቀን ነው።

ልዑል እግዚአብሔር ከበዓሉ በረከት ይክፈለን!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል።
26 viewsbisrat, 16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 19:42:49
91 viewsbisrat, 16:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-16 19:41:50 #ጥር_10_ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ሊጠመቅ_ከገሊላ_ወደ_ዮርዳኖስ_መሄዱ_የሚታሰብበት_በዓል_ነው።

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መሄዱ እየታሰበ የሚከበረው በዓል “ከተራ” በመባል ይታወቃል፡፡

“ከተራ” “ከተረ ከበበ” ከሚለው የግዕዝ ግስ የወጣ ሲሆን ፍቺው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማቆም፣ ማገድ፣ መከልከል” ማለት ነው፡፡

የከተራ በዓል የሚከበረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል አንድ ቀን ሲቀረው በዋዜማው ነው፡፡

ይህም ከጌታችን መድኀኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጥምቀት በዓል አከባበር የሚጀምረው ሁል ጊዜ ጥር 10 ቀን የከተራን በዓል ከማክበር ነው፡፡ በዚህ ዕለት ታቦታቱ ወደ ተዘጋጀላቸው የማደሪያ ቦታ በልዩ ድምቀት በዝማሬ ታጅበው ይወጣሉ፡፡

“ያን ጊዜ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ ዮሐንስ ግን እኔ በአንተ ልጠመቅ እሻለሁ አንተ ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ አይሆንም አለው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ አሁንስ ተው እንዲህ ጽድቅን ሁሉ ልንፈጽም ይገባናልና አለው …”(ማቴ.3፥13) በማለት የኢየሱስ ክርስቶስን ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መሄድ ይገልጻል፡፡ በመሆኑም የበዓሉ ዋዜማ ከተራ በዓል ተብሎ በጾም ታስቦ የታቦታቱን መውጣትና ወደ ማደሪያቸው የመሄድ ሥርዓት በድምቀት የሚከበርበት ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ሥርዓት ነው፡፡

የጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላል፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥል ይውላል፡፡ የምንጮች ውኃ ደካማ በመሆኑ እንዲጠራቀም ይከተራል፡፡ ይህም በየዓመቱ ጥር 10 ቀን የምእመናኑ አብዛኛው ሥራ ውኃውን መከተርና መገደብ በመሆኑ ዕለቱ ከተራ የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ውኃው የሚከተረው በማግሥቱ ጥር 11 ቀን የጥምቀት በዓል ስለሚከበር ለሕዝቡ መጠመቂያ እንዲሆን ነው፡፡ በየሰበካው ቦታ ተለይቶና ተከልሎ ታቦታቱ በዳስ ወይም በድንኳን የሚያድሩበት፣ የተለያዩ የውኃ አካላት ተጠርገው የሚከተሩበት ወይም ሰው ሠራሽ የግድብ ውኃ የሚበጅበት ስፍራ ‹‹ባሕረ ጥምቀት››፣ ‹‹የታቦት ማደርያ›› እየተባለ ይጠራልና ለዚህ ሥርዓት መፈጸም አስቀድሞ በዋዜማ የሚደረግ ዝግጅት ነው፡፡

"የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦትና ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ፥ ከሰፈራችሁ ተነስታችሁ ተከተሉት። " ኢያሱ 3:3

ምስጋና ለእግዚአብሔር ይሁን ለእኛም ከበዓሉ በረከት ይክፈለን!!!
120 viewsbisrat, 16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ