Get Mystery Box with random crypto!

በትናንትናው እለት በአዲስ አበባ በአዲስ አበባ መስተዳድር ስለተፈረሙ በከተማ መስተዳድሩ በጀት እና | B B C News አማርኛ™

በትናንትናው እለት በአዲስ አበባ በአዲስ አበባ መስተዳድር ስለተፈረሙ በከተማ መስተዳድሩ በጀት እና በአለም ባንክ ብድር የሚከናወኑ 3 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ወጪ ስለሚደረግባቸው 3 የመንገድና የድልድይ ግንባታ የተመለከተ መረጃ ነው እነዚህም

1. የመጀመርያው ከአፍሪካ ጎዳና - ኤድናሞል አደባባይ - 22 ማዞሪያ - እንግሊዝ ኢምባሲ

2. ሁለተኛው የአየር ጤና - ወለቴ ሱቅ - አለም ገና አደባባይ

3. የአቃቂ ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክት ናቸው ።
ስለሚሰሩት መንገዶች ያለው እውነታ

• በአጠቃላይ ከ10 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያለው መንገድ ነው፡፡
• ከ15 - 30 ሜትር የጎን ስፋት ያላቸውን 3 የመንገድና የድልድይ ግንባታ ያካተተ ነው፡፡
• ለከተማዋ የመጀመሪያ የሆነውን Intelligent Transport System (ITS) ያካተተ ዲዛይን የተሰራለት ነው፡፡

• የትራፊክ ፍሰትና ቁጥጥር ስርዓቱን ለማዘመን በመከናወን ላይ ከሚገኙ ፕሮጀክቶች አንዱ ነው፡፡
• ከ2.4 – 4 ሜትር ስፋት ያለው የእግረኛ መንገድ አለው፡፡
• 2 ሜትር ስፋት ያለው የብስክሌት ብቻ መሄጃ መንገድ አለው፡፡
• 9 የሳይክል ማቆሚያና 3 የሳይክል መከራያ ቦታዎች አሉት፡፡

• ዘመናዊ የመንገድ መሰረተ ልማትን ታሳቢ ያደረጉ የብልህ የትራንስፖርት ስርዓት አለው።
•10 የመንገድ መጋጠሚያዎች ላይ ሲሲቲቪ ካሜራዎች አሉት።
• 2 ቦታዎች ላይ ዲጂታል የትራፊክ መቁጠሪያዎች አሉት።
• ቅፅበታዊ የአውቶቡስ መረጃ ማግኛ ስርዓቶች አሉት።

• ኦፕቲክ ፋይበርና ዲጂታል ዋይፋይ ባክአፕ አለው።
• መዝናኛ ቦታ ተካቷል።
የህዝብ መጸዳጃ ቤቶች ግንባታ እና የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታ ማሻሻያ
• የፈጣን አውቶብስ መስመር (BRT B-7) አካቷል፡፡
......................
@bbc_amharic1