2022-08-03 21:45:58
አወሊያ ሙስሊም ት/ቤቶች
የ2015 የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ከዕሮብ ሐምሌ 13/2014 ዓ/ል ይጀምራል፡፡
የምዝገባ ቀናትና ሰዓት
ዘውትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ጠዋት ከ2፡30 - 6፡30 ከሰዓት በኋላ ከ8፡00 - 9፡30 ሲሆን
ለነባር ተማሪዎች
1. ከሐምሌ 13/2014 እስከ ሐምሌ 30/2014 ያለ ቅጣት
2. ከነሐሴ 01/2014 እስከ ነሐሴ 30/2014 ከ200 ብር ቅጣት ጋር
3. ነባር ተማሪዎች ለምዝገባ ሲመጡ 1 ጉርድ ፎቶና ሪፖርት ካርድ(ሰርተፌኬት) ይዘው መምጣት አለባቸው፡፡
ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች
ለጀማሪ (ነርሰሪ) የኬጂ ተማሪዎችና ለ1ኛ ክፍል ከሐምሌ 13/2014 ጀምሮ
ለሌሎች ክፍሎች ከሐምሌ 25/2014 እስከ ነሐሴ 30/2014
ለክልላዊ ፈተና ተፈታኞች ውጤት ከተገለፀበት ዕለት ጀምሮ ባሉት 5 የስራ ቀናት ውስጥ
ለአፀደ ህፃናት አዲስ ተማሪዎች በምዝገባ ጊዜ መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
ዕድሜያቸው 4 ዓመት የሞላ
የልደት(የክትባት) ሰርተፊኬት ዋናውን እና ኮፒ
የተማሪው ሁለት ጉርድ ፎቶ-ግራፍ
የወላጅ አንድ ጉርድ ፎቶ-ግራፍ
አንድ ክላሰር
ከአፀደ-ህፃናት ውጪ ላሉ አዲስ ገቢ ተማሪዎች በምዝገባ ጊዜ መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
አማካይ ውጤት 65 እና ከዛ በላይ
ያላቋረጠና ያልደገመ፡፡
ሲማር ከነበረበት ት/ቤት በዲሲፒሊን ግድፈት ያልተባረረ መሆኑንና ጥሩ ስነ-ምግባር ያለው ስለመሆኑ የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል
መሸኛና ሌሎች የትምህርት ማስረጃዎችን አሟልቶ ማቅረብ የሚችል
ት/ቤቱ ያዘጋጀውን የመግቢያ ፈተና ያለፈ
የተማሪው ሁለት ጉርድ ፎቶግራፍ
የወላጅ አንድ ጉርድ ፎቶግራፍ
አንድ ክላሰር
ለቅናሽ ክፍያ የሚያበቁ መስፈርቶች
የዓመቱን ክፍያ በአንድ ጊዜ ለሚከፍሉ 10 % ቅናሽ
በት/ቤቱ ውስጥ 3 ልጅ ለሚያስተምሩ ለአንድ ልጅ 20% ቅናሽ
በት/ቤቱ ውስጥ 4 ልጅ ለሚያስተምሩ ለአንድ ልጅ 30% ቅናሽ
በት/ቤቱ ውስጥ 5 ልጅ ለሚያስተምሩ ለአንድ ልጅ 50% ቅናሽ
6 እና ከ6 ልጅ በላይ ለሚያስተምሩ 1 ልጅ በነፃ
የምዝገባ ቦታዎች
ዊንጌት አልፎ አስኮ መንገድ ላይ በሚገኘው አወሊያ ግቢ (ከአፀደ-ህፃናት አስከ መሰናዶ)
አወሊያ ቁ.1 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ፒያሳ ቅርጫፍ (ከ1ኛ - 8ኛክፍል)
አወሊያ ቁ.2 ት/ቤት ዘነበ ወርቅ ቅርንጫፍ (ከአፀደ-ህፃነት እስከ 10ኛ ክፍል)
ማሳሰቢያ
1. በምዝገባ ወቅት የመመዝገቢያና የመስከረም ወር ወርሃዊ ክፍያ እና የመማሪያ መጽሃፍ ግዢ ክፍያ በሙሉ መፈጸም ይኖርበታል፡፡
2. ት/ቤቱን ለመልቀቅ መሸኛ የሚጠይቁ ወላጆች ከሐምሌ 15/2014 እስከ ሐምሌ 30/2014 ድረስ 100 ብር በመክፈል መውሰድ የሚችሉ ሲሆን ከነሐሴ 01/2014 ጀምሮ ደግሞ 300 ብር ቅጣት በመክፈል መልቀቂያ እንዲወስዱ ይደረጋል፡፡
3. ዩኒፎርም
ለሴቶች ጥቁር በ “A Shape” የተሰፋ፣ ስፌት የማያጣብቅ እና ጉርዱ ቁርጭ ጭሚት ድረስ የረዘመ መሆን አለበት፡፡
ለወንዶች ጠባብ(ቃሪያ/ስኪኒ) ያልሆነና የእግሩ ስፋት 18 ሳ.ሜ መሆን አለበት፡፡
ለበለጠ መረጃ
ቀጥሎ ባሉት ስልክ ቁጥሮች ይደውሉ
አስኮ አወሊያ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል
(09 13 85 84 32 / 09 13 12 51 46)
አስኮ አወሊያ 2ኛ ደረጃና መሰናዶ
(09 11 74 60 21 / 09 24 55 58 71)
ፒያሳ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል
(09 14 50 01 16 / 09 20 51 67 23)
ዘነበ ወርቅ ከኬጂ እስከ 10ኛ ክፍል
(09 13 08 77 75 / 0913 02 48 14/ 09 12 48 93 97)
አስኮ አወሊያ አፀደ-ህፃናት
(09 13 49 18 48/ 0912 44 86 90)
የምዝገባ ክፍያ
1. ለነባር ተማሪዎች መመዝገቢያ 250 ብር
2. ለአዲስ ተማሪዎች መመዝገቢያ 250 ብር
3. ከት/ቤቱ መልቀቂያ ለሚወስዱ ተማሪዎች (ያለ ቅጣት) 100 ብር
4. ከት/ቤቱ መልቀቂያ ለሚወስዱ ተማሪዎች (በቅጣት) 300 ብር
5. ለመግቢያ ፈተና መውሰጃ 50 ብር
ወርሃዊ ክፍያ
1. ለአፀደ ህፃናት (አስኮ ቅርንጫፍ) 1000 ብር
2. ከ1ኛ አስከ 4ኛ ክፍል (አስኮ እና ፒያሳ ቅርንጫፍ) 900 ብር
3. ከ 5ኛ እስከ 8ኛ ክፍል (አስኮ እና ፒያሳ ቅርንጫፍ) 950 ብር
4. ከ 9ኛ እስከ 10ኛ ክፍል (አስኮ ቅርንጫፍ) 1000 ብር
5. ለ11ኛ እና 12ኛ ክፍል (አስኮ ቅርንጫፍ) 1050 ብር
6. ለአፀደ ህፃናት (ነስር ቅርንጫፍ) 950 ብር
7. ከ1ኛ አስከ 4ኛ ክፍል (ነስር ቅርንጫፍ) 850 ብር
8. ከ 5ኛ እስከ 8ኛ ክፍል (ነስር ቅርንጫፍ) 900 ብር
9. ከ 9ኛ እስከ 10ኛ ክፍል (ነስር ቅርንጫፍ) 950 ብር
አወሊያ ት/ቤት ቴሌግራም
t.me/awoliaschool5
1.5K viewsKalid Somalew, 18:45