Get Mystery Box with random crypto!

ዐውደ ምሕረት

የቴሌግራም ቻናል አርማ awedimeherit — ዐውደ ምሕረት
የቴሌግራም ቻናል አርማ awedimeherit — ዐውደ ምሕረት
የሰርጥ አድራሻ: @awedimeherit
ምድቦች: ብሎጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.24K
የሰርጥ መግለጫ

"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-25 11:14:12 #በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ገብርኤል ነኝ ሉቃ ፩÷፲፱

ቅዱስ ገብርኤል በኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ዘንድ ከፍ ያለ መወደድ ያለው መልአክ ነው::ኦርቶዶክሳውያን የክርስቶስ የሆነ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤልን አብዝተን የምንወድበት ብዙ ምክንያቶች አሉን

፩. ቤተሰብኡን የሚጠላ ማን አለ ?

ክርስቲያኖች ከቅዱሳን መላእክት ጋር የአንድ ቤተሰብእ ሀገር አባላት አካላት ነን:: በሐዋ ፱÷፲፭ መምህረ አሕዛብ ብርሃነ ዓለም ተብሎ የተመሠከረለት ቅዱስ ጳውሎስ "እናንተ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና (ባለሀገሮችና) ቤተሰቦች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም" እንዳለ ኤፌ ፪:፲፱:: ሐዋርያው በዚህ ክፍል ቅዱሳን ከተባሉ መላእክት ጋር ቤተሰብእ እንደሆንን ነገረን ሀገራችንም አንድ መሆኑን ሲመሠክር "ከእነርሱ ጋር ባለሀገሮች ናችሁ " አለን:: ሀገራችን የት ነው ? ብለን ብንጠይቅም ራሱ በፊልጵዩስ መልእክቱ "ሀገራችን በሰማይ ነው" ብሎናል ፊልጵ ፫፥፲፰-፲፱ ::የመላእክት ሀገር መንግሥተ ሰማይ እንደሆነ የእኛም ሀገር በሰማይ ነው::ሐዋርያው "እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም" ያለው ቅዱስ ጴጥሮስ "እንግዶችና መጻተኞች ናችሁ" ፩ጴጥ ፪:፲፩ ብሎ በዚህ ኃላፊ ዓለም እንግዶች መሆናችንን የገለጠበትን የዚህ ዓለም እንግዳነታችንንና መጻተኛነታችንን ሳይሆን በሰማይ መንግሥት እንግዶች አለመሆናችንን ለመግለጥ ነው:: ይህ ዓለም ቢበዛ 70 ቢበረታም 80 ዘመን ብቻ የምንኖርበት ጊዜያዊ መኖሪያችን ነው መዝ 89÷10 ::ቅዱሳን መላእክት ቤተሰቦቻችን (እንደ ወንድም አባት እናት እህት) ስለሆኑ በአንዳችን የልብ ንስሐና መመለስ እንኳን ተደስተው በሰማይ ሀሴትን ያደርጋሉ ይዘምራሉ ያሸበሽባሉም :: ይህም የጌታችን በሥጋዌው ወራት ምሥክርነት ነበር ሉቃ ፲፭:፲::ቅዱሳን መላእክት ከምእመናን የማይለዩ እንደ እውነተኛ ወንድም አሳቢ እንደ አባት ጠባቂና ከክፉ የሚያድኑ አገልጋዮችም ናቸው:: መዝ 90÷11 ዳን 4÷12 የሐዋ 12÷5 የሐዋ 27÷23

2. ቅዱስ ገብርኤል መምህራችንም ነው

ቅዱስ ገብርኤል በቅዱሳት መጻሕፍት ከተገለጡልን ሥራዎቹ አንዱ የቅዱሳን ነቢያት እንዲሁም ምእመናን አስተማሪ መካሪ ጥበብ ገላጭ መሆኑ ነው :: እስከ ምጽአተ ክርስቶስ ሊሆን ያለውን ነገር በምልአት በስፋት የተናገረ ነቢዩ ዳንኤል "ገብርኤል ወደ እኔ እየበረረ መጣ በማታም በመሥዋእት ጊዜ ተናገረኝ አስተማረኝም እንዲህም አለኝ ዳንኤል ሆይ ጥበብና ማስተዋልን እሰጥህ ዘንድ አሁን መጥቻለሁ" ዳን 9:22 እንዳለ :: ቅዱስ ገብርኤል ምሥጢርን ጥበብን የመግለጥ ጸጋ ሀብት እንደተሰጠው ትመለከታላችሁን ? ዛሬ ላለን ምእመናን የክርስቶስ እናቱ እመቤታችንን "ጸጋን የሞላብሽ ሆይ ደስ ይበልሽ" እያልን እናመሰግናት ዘንድ ያስተማረን እርሱ አይደለምን ? ሉቃ 1:26-40 :: "በገብርኤል ሰላምታ ሰላም እንልሻለን" ማለታችንም ለዚሁ ነው::

3 . አረጋጊ አጽናኝ ፍርሃትንም የሚያርቅ መልአክ ነው

አንዱ የቅዱስ ገብርኤል ሥራ ፍርሃትን ማራቅ የታወኩትንም ማረጋጋት ነው :: ስለሆነም ወደ ሰዎች በመጣ ጊዜ "አትፍሩ" እያለ ያረጋጋቸዋል :: እንኮዋ በዚህ ዓለም ሀሳብና የሥጋ ነገር የታወክነውን ቀርቶ መንፈሳዊውን ሰው ነቢዩ ዳንኤልን "አትፍራ" ብሎ ፍርሃትን አርቆለታል ዳን 8:15 ; 10:12 :: የአምላክ እናት ድንግል ማርያምንም ሲያበሥራት "ማርያም ሆይ አትፍሪ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋን አግኝተሻልና" ሉቃ 1:29-40 እያለ ነበር ::

4 . ስለ ምእመናን በእግዚአብሔር ፊት በባለሟልነት የሚቆም (የሚለምን የሚማልድ) መልአክ ነው "እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆም ገብርኤል ነኝ" እንዳለ ሉቃ 1:19

5 . ደጋግ ሰዎችን ለንስሐ እንዲበቁ ከስህተታቸው እንዲታረሙ እንደ አባት የሚቀጣ መልአክ ነው :: ካህኑ ዘካርያስን ዲዳ እንዲሆን እንደቀጣውና ልጁ በተወለደ ጊዜም አንደበቱ እንደሚፈታለት እንደነገረው መጽሐፍ ይነግረናል ሉቃ 1:19-25 :: "ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት በፊቱም ተጠንቀቁ" ተብሎም ከኃጢአታቸው የማይመለሱትን እንደሚቀጣ ተነግሮናል ዘጸ 23:20

6 . በእባቦች ላይ በገነትም ባሉ ጻድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ገብርኤል ነው ተብሎም ተነግሮናል ሔኖክ 6:7-8 :: እንግዲህ ምን እንላለን ? የመላእክት አለቃ የአብሣሬ ትስብእት የቅዱስ ገብርኤል ጥበቃ አይለየን አሜን!!

#ቢትወደድ ወርቁ
የካቲት 18 ቀን 2011 ዓ ም
ድጋሚ የተለጠፈ
1.3K viewsተርቢኖስ ሰብስቤ ምንዳ, 08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 11:10:10
1.0K viewsተርቢኖስ ሰብስቤ ምንዳ, 08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 21:23:34
577 viewsተርቢኖስ ሰብስቤ ምንዳ, 18:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 11:32:57 በእርግጥ ኃይለ ቃሉ ለልጇ ለወዳጅዋ ለጌታችን ለመድኃኔታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረ ነው።

#ሆኖም ግን ለእርሷም ይሆናል ። የልጅ ሁሉ ነገር ለእናትም ጭምር ነውና።በቤተልሔም በከብቶች ግርግም በወለደችሁ ጊዜ ሰባ ሰገል እጅ መንሻ ስጦታን ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤን አምጥተውለት ነበር። ወርቅ ጽሩይ (የጠራ ፣የነጻ፣ ንጹሕ) እንደሆነ አንተም ጽሩይ ባሕሪ ነህ ሲሉ። ዕጣንም አመጡለት ሊቀ ካህናት ይባላልና፤ ከርቤንም አመጡ ከርቤ መራራ ነው መራራ ሙትን ትሞታለህ ሲሉ።

ሆኖም ይህ ስጦታ እናቱን አይመለከታትም ማለት አይደለም ልደቱን የሚያከብር አንድ ልጅ ምንም እንኳን ልደቱ የእርሱ ቢሆንም ስጦታው ግን እናቲቱንም ይመለከታል። ልጁማ የስጡታውን መንነትና ትርጉም ላይረዳ ይችላል። እናት ግን ጠንቅቃ ታውቀዋለች። " #ማርያም ግን ይህን ነገር ሁሉ እያሰበች በልቧ ትጠብቀው ነበር " #ሉቃ 2÷19

#ስለዚህ የሰባ ሰገል ስጦታ እንኳን ወርቅ ዕጣን ከርቤ ልጇን ብቻ ሳይሆን እናቲቱ ድንግል ማርያምንም ይመለከታል። ወርቅ ንጽሑ የጠራ ነው። ንጽሐ ጠባይ አላደፈብሽም ሲሉ ወርቅ አመጡላት አንድም ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችን የኃጢያት ጭቃ ካቆሸሻቸው ከሰዎች ወገን ተገኝታለች ግን ጭቃ አይደለችም ። ዕጣንም አመጡ ዕጣን ምሁዝ (መልካም መሐዛ ያለሁ) ነው። እመቤታችንም ምሁዚት ማሕዛዋ ያማረ መልካም ዕጣን ነች ክርስቶስ ክርስቶስን ትሸታለችና። #ዕጣን_ይእቲ_ማርያም እንዲላት ሊቁ ።

ከርቤም አመጡላት ከርቤ የተለያዮትን አንድ አድርጎ ያጣብቃል ስለዚህ የፍቅር ምሳሌ ነው። ከርቤ እንዲያጣብቅ ፍቅር የሆነች ድንግል ማርያምም ወልድ ክርስቶስን ንጽሐ ሥጋዋን፣ ንጽሐ ነፍሷን ፣ ንጽሐ ልቡናዋን በማጽናት ወልድ ክርስቶስን ከመንበሩ ሥባ ሰው አምላክ፣ አምላክ ሰው ሆኖ ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕሪ አንድ ባሕሪ ከሁለት ፈቃድ አንድ ፍቃድ እንዲሆን ያደረገች የፍቅር ሰንሰለት የተዋሕዶ መዲና ናትና ከርቤ አመጡላት ። ንጉሥ ውበትሽን ወድዶአልና፥ እርሱ ጌታሽ ነውና። የጢሮስ ሴቶች ልጆች እጅ መንሻን ይዘው ይሰግዱለታል። የምድር ባለጠጎች አሕዛብ በፊትህ ይማለላሉ ። #መዝ 45÷11-12
#አንድም ከርቤ መራራ ነው። በልጅሽ ምክንያት መራራ ሐዘን ያገኝሻል ሲሉ መራራውን ከርቤን አመጡ። ይህ ብቻ አይደለም ተንበርክከውም ለልጇ የባሕር ለእርሷ ደግሞ የጸጋ ስግደትን አቅርበዋል። ስለዚህ ለልጅ የተደረገ ሁሉ ለእናት ደግሞ ተደረገ።

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤” ብሎ ክርስቲያኖች ኑሯቸውና ሞታቸው ክርስቶስ የመሰለ ክርስቶስን የተባበረ ከሆነ ትንሣኤያቸውም የክርስቶስን የመሰለ ወይም የተባበረ ትንሳኤ እንደሚኖራቸው ጽፏል ። #ሮሜ 6፥5

#ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ እርሷን የመሰላት የክርስቶስ እናቱ የድንግል ትንሣኤማ እንዴት አብልጦ ከልጇ ትንሳኤ ጋር የተባበረ የተመሳሰለ መሆኑን መገመት ቀላል ነው ። ስለዚህ ሕያዊትን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጓታላችሁ ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም ብንል ትክክል ነን። ሞቷ እንደልጇ ሞት ትንሳኤዋም እንደልጇ ያለ ትንሣኤ ነውና።
ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሴን ላኖራትም ላነሳትም ሥልጣን አለኝ እንዳለና አባት ሆይ ነፍሴን በእጄ አደራ እሰጣለሁ ብሎ በፍቃዱ ነፍሱን እንደሰጠ እርሷም ከዚህ ዓለም ድካም ስታርፍ ፍቃዷን ተጠይቃለች እንጂ የሞት እንግድነት እርሷን አላስደነገጣትም ። #ዮሐ 10፥17 # ሉቃ 23፥46
#ሞት ማንንም አያስፈቅድም እርሷን ግን በእኔ ሞት ነፍሳት ከሲዖል የምታወጣልኝ ከሆነማ አንድ ጊዜ አይደለም ሰባት ጊዜ ልሙት እስክትል ድረስ ፍቃዷን ቆሞ ጠበቋል። የልጇ ሞት ነፍሳትን ከሲዖል ወደ ገነት ያጋዘ ነፃ ያወጣ እንደሆነ የእርሷም ሞት ነፍሳትን ወደ ገነት መልሷል፤ ልጇ በከርሰ መቃብር ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት ቆየቶ በሦስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ እንደተነሳ እርሷም ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በምድር ልብ ውስጥ ቆይ እንደልጇ ባለ ትንሣኤ በክብር በይባቤ በመላእክት ምስጋና ተነስታለች ።
#ልጇ ወደ አባቱ እንዳረገ እርሷም ወደ ልጇ ዐርጋለች።ልጇ በአባቱ ቀኝ በሥልጣን እንደተቀመጠ እርሷም በልጇ ቀኝ በክብር በሥልጣት ማር ይቅር በል እያለች በአማላጅነት ንግሥቱቱ ቆማለች።“የንጉሦች ሴት ልጆች ለክብርህ ናቸው፤ በወርቅ ልብስ ተጐናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች ። ” #መዝ45፥9
ወዳጄ እመቤታችንን ትፈልጋታለህ ?ስለምን ታድያ ከሙታን መንደር ትፈልጋታለህ እንደተነገረላት ተነስታለች እንጂ በዚህ የለችም። “አቤቱ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥ አንተና የመቅደስህ ታቦት።” #መዝ132፥8


አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፲ ፮ / ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
600 viewsተርቢኖስ ሰብስቤ ምንዳ, 08:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 11:32:57
449 viewsተርቢኖስ ሰብስቤ ምንዳ, 08:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 21:51:42
አርጋለች #ማርያም ተነስታለች!
602 viewsተርቢኖስ ሰብስቤ ምንዳ, 18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 16:51:59 ❖ ሌላው ሙሉሙሉ ዳቦ መጋገሩ በትውፊት እንደምንረዳው ጌታ ብርሃኑን ሲገልጽ ብርሃኑ እስከ አርሞንኤም ተራራ ድረስ ያበራ ስለነበር እረኞች ሌሊቱ ኹሉ ቀን መስሏቸው እዛው ስለዋሉ ቤተሰቦቻቸው “ኅብስት” ይዘውላቸው ሄደዋልና የዚያ ምሳሌ እንደኾነ ይነገራል፡፡

[በደብረ ታቦር ላይ ብርሃኑን የገለጠው አምላካችን ክርስቶስ ምስጋና ይግባው]፡፡
[መልካም በዓል]
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
2.7K viewsተርቢኖስ ሰብስቤ ምንዳ, 13:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 16:51:59 [ደብረ ታቦር]
ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
❖ ይኽ በዓል ከጌታችን 9ኙ ዐበይት በዓላት አንደኛው ሲኾን በዓሉ በየዓመቱ ነሐሴ 13 ላይ በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡ ታሪኩ በ3ቱ ወንጌላት ላይ የተጻፈ ሲኾን ጌታችን አምላችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሌሎቹን ሐዋርያትን ከእግረ ደብር (ከተራራው ሥር) ትቶ የምስጢር ደቀ መዛሙርት የሚባሉት፣ በእምነት በተስፋ በፍቅር የሚመሰሉት ሦስቱን (ጴጥሮን፣ ያዕቆብን፣ ዮሐንስን) ይዟቸው ወደ ታቦር ተራራ ወጣ።

የሞተውን ሙሴን ከ1644 ዓመታት በኋላ አምጥቶ፤ የተሰወረውን ኤልያስንም ከብሔረ ሕያዋን አምጥቶ የሕያዋን አምላክና የሙታን አሥነሺያቸው ርሱ መኾኑን የገለጸበት ታላቅ ምስጢር የተከናወነበት ነው፡፡ (ማቴ 17፡1-9)።

❖ ጌታ 8ቱን ሐዋርያት ይዟቸው ያልወጣበት በይሁዳ ምክንያት ነው ምክያቱም ከምስጢረ መንግሥቱ ቢለየኝ ከሞቱ ገባኹበት ባለ ነበርና ነው፤ ነገር ግን በተራራው ላይ ለ3ቱ የተገለጸው ምስጢር ከተራራው ሥር ላሉት ከይሁዳ በስተቀር ተገልጾላቸዋል፤ ለእኛም እንደ ሐዋርያት ምስጢሩን ጥበቡን ይግለጽልን፡፡

❖ ብዙ ተራሮች ሳሉ የታቦር ተራራን የመረጠበት
1)አስቀድሞ የጌትነት ክብሩ በዚያ ተራራ ላይ እንደሚገልጽ ነቢዩ ዳዊት በመዝ 88፡12 ላይ፦ “ታቦር ወአርሞንኤም በስመ ዚኣከ ይትፌሥሑ” (ታቦርና አርሞንኤም በስምህ ይደሰታሉ) በማለት ጌታ በዚያ ተራራ ላይ ብርሃኑን ሲገልጽ የብርሃኑ ነጸብራቅ እስከ አርሞንኤም ተራራ ድረስ እንደሚታይ የተናገረውን ትንቢት ለመፈጸም ነው፡፡

❖ ሌላው ታቦር በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ 12 ጊዜያት ሲጠቀስ በተለይ በመሳ 4 እና 5 ላይ እንደተጻፈው አስቀድሞ በብሉይ ኪዳን የእስራኤል ጠላት የነበረው ሲሳራን መስፍኑ ባርቅ በተራራው ላይ ድል ነሥቶበት ነቢይቱ ዲቦራም በተራራው ላይ በደስታ አመስግናበታለች ዘምራበታለች። በተመሳሳይ መልኩ የእስራኤል ዘነፍስ የክርስቲያኖችን ጠላት የኾነውን ዲያብሎስን የኹላችን ፈጣሪ ንጉሠ ነገሥት ኢየሱስ ክርስቶስ በተራራው ላይ አምላክነቱን ገልጦ ድል ስለነሣው ነቢያት ሐዋርያት ምእመናን የሚያመሰግኑት ስለኾነ ለምሳሌነቱ ተስማሚነት ያለውን የታቦርን ተራራን መርጦታል፡፡

❖ ለምን ሙሴንና ኤልያስን ከነቢያት መኻከል መረጠ? ቢሉ፦
ሀ) በማቴ 16፡13 ላይ ሐዋርያትን ስለማንነቱ እንደጠያቃቸው እንደመለሱለት ኹሉ በእውነት ጌታችን የሙሴና የኤልያስ በአጠቃላይ የነቢያት ፈጣሪ የእግዚአብሔር ልጅ መኾኑን ሲገልጽላቸው ነው።

ለ) በዘፀ 33፡17-23 ላይ ሊቀ ነቢያት ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ካለው ጥልቅ ግንኙነት የተነሣ “እባክኽ ክብርኽን አሳየኝ” ብሎ ልመናን አቀረበ፤ እግዚአብሔርም "ወአነብረከ ውስተ ስቊረተ ኰኲሕ ወእከድን እዴየ በላዕሌከ እስከ አኃልፍ" (በሰንጣቃው ዐለት አኖርሃለኍ፤ እስካልፍ ድረስ እጄን በላይኽ እጋርዳለኍ፤ ካለፍኍ በኋላ እጄን አንሥቼልኽ ጀርባዬን ታያለኽ፤ ፊቴ ግን አይታይም) ብሎታል (ዘፀ ፴፫፥፲፯-፳፫)፡፡

❖ ይኸውም ጀርባ በስተኋላ እንደሚገኝ ኹሉ በኋላ ዘመን አካላዊ ቃል ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ በታቦር ተራራ ላይ እንደሚገለጽለት ሲያመለክተው ነው።

❖ ሊቁ ቅዱስ ያዕቆብም ስለ ታቦር በሚተነትነው መጽሐፉ ሙሴ በቃዴስ ባለው በመሪባ ውሃ ከእስራኤል ጋር በበደለው በደል ምክንያት ምድረ ርስት ኢየሩሳሌም እንዳይገባ አይቷት ብቻ በናባው ተራራ ላይ እንዲያርፍ ኾኗል (ዘፀ ፴፪፥፶፪፤ ዘፀ ፴፬፥፩-፰)፡፡

❖ ይኽ ለሙሴ አሳዛኝ ቢኾንም በኋላ ዘመን አካላዊ ቃል ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ሙሴ በፊት በሩቁ ያያት ግን ያልገባባት በምድረ ርስት በኢየሩሳሌም ያለች ታቦር ተራራ ላይ አምጥቶት በዘመነ ብሉይ በአካለ ሥጋ ያልገባባትን ርስት እንዲገባባት አድርጎታል፤ ይኸውም አዳምና ልጆቹ በአካለ ሥጋ ያጡትን ርስታቸው ገነትን በአካለ ነፍሳቸው ዳግመኛ ሊያገባቸው እንደመጣ የሚያመለክት መኾኑን በስፋት አስተምሯል፡፡

❖ ጌታችን በብሉይ ኪዳን ከነበሩት ከነቢያት ሙሴንና ኤልያስን በሐዲስ ኪዳን ከነበሩት ከሐዋርያት ሦስቱን በታቦር ተራራ ላይ ማውጣቱ፦

1) የታቦር ተራራ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ በመኾኗ ሲኾን በቤተ ክርስቲያናችን ብሉይ ኪዳንና ሐዲስ ኪዳን እንደሚነገሩ ለማመልከት

2) በተራራ በተመሰለች በጉባኤ ቤት ብሉይና ሐዲስ እንደሚነገሩ ለመግለጽ፡፡

3) ሌላው የታቦር ተራራ የመንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ስትኾን ይኸውም ጌታ ነቢያትንና ሐዋርያትን በተራራዋ ላይ መሰብሰቡ መንግሥተ ሰማያትን ነቢያትም ሐዋርያትም እንደሚወርሷን ለማመልከት

4) ሙሴ ያገባ ሲኾን ኤልያስ ድንግል ነውና መንግሥተ ሰማያትን ደናግልም ያገቡም እንደሚወርሷት ለማጠየቅ ነው፡፡

5) እንደ ያዕቆብ ዘሥሩግ ትርጓሜ ሙሴ ኦሪት ዘፍጥረትን ሲጽፍ፦ “በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን ፈጠረ” (ዘፍ 1፡1) እንዳለ፤ ዮሐንስም “በመጀመሪያ ቃል ነበር” (ዮሐ 1፡1) ብሎ እንደ ሙሴ አምላክነቱን የሚመሰክር ነውና ሙሴ አስቀድሞ የጻፈልኝ፤ አኹንም ዮሐንስ አምላክነቴን የሚጽፍልኝ እኔ ነኝ ሲል ነው፡፡

6) ሙሴና ኤልያስ ይመሳሰላሉ፤ ይኸውም በሲና ተራራ 40 ቀንና ሌሊት እንደጾመ ኤልያስም በደብረ ኮሬብ 40 ቀንና ሌሊት የጾመ ነውና፨

7) ሙሴ ንጉሡ ፈርዖንን የገሠፀ እንደነበር ኤልያስም ንጉሡ አክዐብን የገሠፀ ነውና፨

8) ሙሴ ከንጉሡ ፈርዖን ፊት ሸሽቶ እንደሄደ ኤልያስም ከንግሥቲቱ ኤልዛቤል ፊት ሸሽቶ ሄዶ ነበር።

9) ዳግመኛም ሰማይኑን ዝናብ እንዳያዘንም በተሰጠው ሥልጣን ባሰረውና ከ3 ዓመት ከ6ወር ቆይታ በኋላ እንዲዘንብ በፈታው ኤልያስን እንዳመጣ ኹሉ የማሰር የመፍታት ሥልጣን ሥልጣነ ተሰጥቶት “እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም የመንግሥተ ሰማያትንም መክፈቻዎች እሰጥሃለሁ፤ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል” (ማቴ 16፡18-19) ላለው ለጴጥሮስን ታላቅ ሰማያዊ ሥልጣን መስጠቱን ለማመልከት አምጥቷቸዋል፡፡

❖ በቤተ ክርስቲያንና በሀገራችን ያለው መንፈሳዊ አከባበር ደማቅ ነው፤ ይኽ በዓል በቤተ ክርስቲያን በማሕሌት በቅዳሴ በትምህርት የሚከበር በዓል ሲኾን በሀገርኛ የቡሄ በዓል ይባላል፤ ቡሔ ማለት ሊቁ ደስታ ተክለ ወልድ በመዝገበ ቃላት ላይ ሲገልጹት ቧ ብሎ በደብረ ታቦር የተገለጠው የጌታችንን የፊቱን ብርሃን ጸዳል የልብሱን እንደ በረዶ ነጭ መኾን ያስረዳል ስለዚኽ የብርሃን፣ ብርሃናዊ ማለት ነው፡፡

❖ በዚህ በዓል በታቦር የታየው የብርሃኑ ምሳሌ የሚሆን ችቦ ይበራል፤ ሌላው በዚኽ በዓል ሰሞን በገጠር ከተራራ ላይ እረኞች ሕጻናት ዥራፍ እየገመዱ ማስጮኻቸው ጌታ በተራራ ላይ ብርሃኑን በገለጸ ጊዜ አብ በደመና ኾኖ “እርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት” ባለ ጊዜ ሐዋርያት በድምፁ ደንግጸው መውደቃቸውን ለማመለክት ነው፡፡

ጌታችን ጌትነቱን ገልጦበታል። የአብ ድምፅ ተሰምቶበታልና ታቦር ተራራ ቅዱስ ነው። ቅዱስ ጴጥሮስም በመልእክቱ "ከገናናው ክብር፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው የሚል ያ ድምፅ በመጣለት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ምስጋናን ተቀብሎአልና፤ ¹⁸ እኛም በቅዱሱ ተራራ ከእርሱ ጋር ሳለን ይህን ድምፅ ከሰማይ ሲወርድ ሰማን።" በማለት ገልጦታል (2ኛ ጴጥ 1:17-18)
2.9K viewsተርቢኖስ ሰብስቤ ምንዳ, 13:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 16:51:47
1.6K viewsተርቢኖስ ሰብስቤ ምንዳ, 13:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ