#MizanTepiUniversity ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ አዲስ አመራር ተመድቦለታል። ዋቆ ገዳ (ዶ/ር) የሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ሆነው በትምህርት ሚኒስቴር ተመድበዋል። ተረፈ ጌታቸው (ዶ/ር) ተጠባባቂ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት፣ ግርማ ጥላሁን (ዶ/ር) ተጠባባቂ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት እንዲሁም ይደግ ማሞ ተጠባባቂ የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ እና የቢዝነስ ልማት ም/ፕሬዝዳንት ሆነው መመደባቸው ተገልጿል። አዲስ የተመደቡት አመራሮች ለአንድ ዓመት ተቋሙን እየመሩ እንደሚቆዩና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ምልመላ መመሪያ መሠረት ወደፊት በሚወጣ የውድድር ማስታወቂያ የቋሚ አመራሮች ምርጫ ይደረጋል ተብሏል። ለጥቆማ @atc_newsbot https://t.me/atc_news 17.0K viewsMuJa. M, 16:51