Get Mystery Box with random crypto!

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብ | ATC NEWS

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ ጋር በመተባበር ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች የማጠናከሪያ ትምህርት መስጠት ሊጀምር ነው፡፡

የማጠናከሪያ ትምህርቱ በሀዲያ ዞን፣ በከምባታ ዞን እና በጠምባሮ ልዩ ወረዳ ለሚገኙና ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለሚወሰዱ ተማሪዎች እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡

ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና ከሁለቱም ዞኖች ከሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተመረጡ 432 መምህራን በ54 ማዕከላት ከመጪው ቅዳሜ ጀምሮ ለተከታታይ ስምንት ሳምንታት የማጠናከሪያ ትምህርቱን ይሰጣሉ ተብሏል፡፡

የማጠናከሪያ ትምህርቱ የተፈታኝ ተማሪዎችን የማለፍ ምጣኔ ለማሳደግ እንደሚያስችል ታምኖበታል፡፡

ለጥቆማ @atc_newsbot
https://t.me/atc_news