Get Mystery Box with random crypto!

(የሉቃስ ወንጌል ምዕ. 9) ---------- 31፤ በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው | የእውነት ሚዛን(ቴቄል)

(የሉቃስ ወንጌል ምዕ. 9)
----------
31፤ በክብርም ታይተው በኢየሩሳሌም ሊፈጽም ስላለው ስለ መውጣቱ ይናገሩ ነበር።

32፤ ነገር ግን ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት እንቅልፍ ከበደባቸው፤ ነቅተው ግን ክብሩንና ከእርሱ ጋር ቆመው የነበሩትን ሁለት ሰዎች አዩ።

ስታንቀላፋ ቅዱሳንን አታይም ክርስቶስንም አታይም ስታቀላፋ ፕሮቴስታንት ትሆናለህ ስትነቃ ቅዱሳንን ታያለህ ፤ክርስቶስን ታያለህ ኦርቶዶክስም ትሆናለህ
ከክርስቶስ ጋ ከሆንክ ቅዱሳንን በሥጋ ከዚህ ምድር የተለዮትን በክብር ታያቸው አለህ
ከክርስቶስ ስትለይ ቅዱሳን ሙተዋል በኛ ዘንድ የሉም ምንም አያውቁም አይናገሩም ምንም አይሠሩም ትላለህ
ከክርስቶስጋ ስትሆን በሥጋ ሞተ ከዚህ የተለዩት ትንቢት ሲናገሩ ታያለህ ።
የፕሮቴስታንቱ ዓለም በእንቅልፍ ውስጥ ስለሆነ በዚህ ቡድን ውስጥ ያለ ሰው ክርስቶስን ማዬት አይችልም ቅዱሳንን ማዬት አይችልም በዚህ ቡድን ውስጥ ያለ ሰው ከክርስቶስ የተለዬ ስለሆነ ክርቶስን አያይም ቅዱሳንን አያይም ።ለዚህም ነው ቅዱሳን ምንም አያቁም በሥጋ ከተለዩ በኋላ አያማልዱም አብረውን አይሆኑም አናያቸውም የሚሉት ምክንያቱም በእንቅልፍ ቅስጥ ናቸው ከክርስቶስም የተለዩ ናቸው ።
እነ ጴጥሮስንና ከእርሱ ጋር የነበሩት በእንቅልፍ ውስጥ ሳሉ ሳይሆን ቅዱሳንን ያዩት ከእንቅልፋቸው ሲነቁ ነው ።በዚህ መጽሐፍ ከክርስቶስጋ ከሆነን እና በእንቅልፍ ውስጥ ካልሆንን ክርስቶስንም ቅዱሳንንም በክብር ማዬት እንዴምንችል አስረዳን
@felgehaggnew
@felgehaggnew