Get Mystery Box with random crypto!

አ/ተ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል

የቴሌግራም ቻናል አርማ anketset — አ/ተ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል
የቴሌግራም ቻናል አርማ anketset — አ/ተ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል
የሰርጥ አድራሻ: @anketset
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 422

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2022-07-25 18:49:32 ሐምሌ 19

በዓሉ ለቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት


ገብርኤል ማለት እግዚእ ወገብር / አምላክ እና ሰው ማለት ነው። በዕለተ እሑድ መላእክት መኑ ፈጠረነ ሲሉ ዲያብሎስ እኔ ፈጠርኳችሁ ብሎ ፈጥሮ ለማሳየት እጁን ከእሳት ከትቶ አቃጥሎት መላእክት በተረበሹ ጊዜ በያለንበት እንቁም ብሎ ያረጋጋቸው መልአክ ነው ። በዚህም ምክንያት ጌታ '' ወበእንተዝ ይደልዎ ከመ ይጹር ዜናሃ ለማርያም '' እንዲል ሥጋዌውን ለድንግል እንዲያበስር አድሎታል ። ከዚህም በኋላ ደጋግ ሰዎችን ለመርዳት የሚወጣ የሚወርድ ሆኗል።

በዚህም ዕለት የእግዚአብሔር አገልጋዮች የሆኑትን ሕፃኑን ቂርቆስና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣን አድኗቸዋል። ቅዱስ ቂርቆስ አገሩ ሮም አንጌቤን ነው አባቱ ቆዝሞስ ይባላል እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ በትውልዷ ከአዝማደ ነገሥት ነች። ዲዮቅልጥያኖስ በነገሠ በ20 ዓመት በአባ ባጋግዮስ ምክንያት '' አብያተ ጣዖታት ይትራኀዋ ወአብያተ ክርስቲያናት ይትዐጸዋ '' / የጣዖትታት ቤቶች ይከፈቱ አብያተ ክርስቲያናት ይዘጉ / ብሎ አወጀ /በ303 ዓ.ም. / በዚህ ጊዜ እኩሎቹ ተሰደዱ ቅድስት ኢየሉጣም ልጇ የ3 ዓመት ሕፃን ነበርና ለርሱ ብላ ወደ ኢቆንዮን ሸሸች ።

መስፍነ ብሔሩ ( የአገሩ ገዢ) እለእስክንድሮስ ክርስቶስን ካጂ ለጣዖት ስገጂ አላት ፤ ዓይን እያለው ለማይሰማ በቃልህ አዘህ በእጅህ ሠርተህ ላቆምከው ምስል አልሰግድም አለች። አይሆንም ካልሽማ በሰይፍ ትቀጪያለሽ ብሎ አስፈራራት። እስኪ ይህን ሕፃን ጠይቀው አለችው። አንተ ሕፃን ወርቅ እሰጥሀለሁ ለዚህ ጣዖት ስገድ አለው መንፈስ ቅዱስ አድሮበታልና አንሰ ኢይሰግድ ለአማልክቲከ ርኩሳን ዘኢይክሉ አድኅኖ ርእሶሙ/ ራሳቸውን እንኳ ማዳን ለማይችሉ ርኩሳን ጣዖታትህ አልሰግድም አለው ተበሳጨ በብረት ጋን ውኃ አፍልታችሁ ከዚያ ውስጥ ጣሏቸው አለ ዝፍት ተይ ጨምረው አንድደው በብረት ጋን ውኃ አፈሉ ። ድምጻ ለጽሕርት ከመ ነጎድጓደ ክረምት ይላል የውኃው ፍላት እንደ ክረምት ነጎድጓድ 42 ምዕራፍ ድረስ ይሰማ ነበር ። ሊከቷቸው ሲወስዷቸው ኢየሉጣ ልቧ በፍርሀት ታወከ እሱ ግን ፍርሃቷን አርቅላት እያለ ይጸልይላት እሷንም ጥብዒኬ እምየ እምዝ ዳግመ ኢይረክበነ ሞት ሁለተኛ ሞት አያገኘንምና እናቴ ሆይ በርቺ ጨክኚ በዚያውስ ላይ ዘአድኀኖሙ ለአናንያ ወአዛርያ ወሚሳኤል ውእቱ ያድኅነነ አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን ያዳነ እኛንስ ያድነን የለምን እያለ እያጽናናት ልብሷን እየጎተተ ከእሳቱ ቀረቡ ከዚህ በኋላ እሷም ጨክና በፍጹም ልብ ሆነው ተያይዘው ከእሳቱ ከውኃው ገብተዋል ። በዚህ ጊዜም ከዐላውያን ነገሥታት ከዐላውያን መሳፍንት ገብተው የመሰከሩለት በስሙ መከራ የተቀበሉለት ጌታ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ በበትረ መስቀሉ እሳቱን አጥፍቶ የፈላውን ውኃ አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል ። ይህም የኾነው በሐምሌ 19 ቀን ነው ፤ በወጡም ጊዜ ልብሳቸው ሳይለበለብ ሰውነታቸው ሳይሸበሸብ ቢያዩ ከአሕዛብ ብዙዎቹ አምነው አንገታቸውን ለስለት ሥጋቸውን ለእሳት ሰጥተው በሰማዕትነት ዐርፈዋል።

ከዚህም በኋላ እለእስክንድሮስ መከራውን ፈርተው ይመለሳሉ ብሎ በሀብለ ሰናስል እያሰረ በችንካር እየቸነከረ ሲያሰቃያቸው ቆየ ። የማይሆንለት ቢሆን እጅ እግራቸውን አስሮ ከዝግ ቤት አስቀመጣቸው ። ጌታም የመከራቸውን ጽናት የትዕግሥታቸውን ብዛት አይቶ በጥር 15 ቀን ሕፃኑ ቂርቆስን በጥር 16 ቀን እናቱ ቅድስት ኢየሉጣን በሰማዕትነት ከመከራው አሳርፏቸዋል ።

ምንጭ ፦ መዝገበ ታሪክ ክፍል አንድ እና ሁለት

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር
80 views15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 20:30:01 ለካልኣይ ተማሪዎች
እሑድ 10/11/2014 ካልኣይ ተማሪዎች ትምህርት ስለማይኖር ከወዲሁ እንድታውቁ
እና 11 : 30 ሰዓት ላይ መምጣት የምትችሉ ተማሪዎች በጥያቄ እና መልሱ መርሐ ግብር ላይ ተገኝታችሁ ብዙ ዕውቀት እንድታተርፉ ተጋብዛችኋል ።
104 viewsedited  17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 23:07:55 ሐምሌ 7 -- በዓለ አጋእዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ

ሥላሴ የሚለው ሠለሰ - ሦስት አደረገ ከሚለው የግዕዝ ሥርወ ቃል የተገኘ ሲሆን ሦስት (ሦስትነት ) ማለት ሲሆን በያዘው ምሥጢር ግን አንድም ሦስትም / አንድነት ሦስትነት ተብሎ ይተረጎማል ።
ሦስትነታቸው በስም ፣በአካል፣ በግብር አንድነታቸው በባሕርይ ፣ በህልውና በመለኮት ፣ በሥልጣን በፈቃድ ነው ።

ሀ,የስም ሦስትነት - አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ብሎ ነው ማቴ 28 ፣ 19

ለ, የአካል ሦስትነት - ለአብ ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፣ ለወልድም ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፣ ለመንፈስ ቅዱስም ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ አለው።
አካል ከራስ ፀጉር እስከ እግር ጥፍር ያለው ነው ። ገጽ ፊት ነው መልክም ከራስ ፀጉር እስከ እግር ጥፍር ያለ ነው
አካልም እንዳላቸው ሲያጠይቅ መዝ 33 ፥ 15, መዝ 118+73
ኢሳይያስም '' ሰማይኒ መንበርየ ወምድርኒ መከየደ እገርየ '' ብሏል (ኢሳ 66 + 1 ) ለአብርሃም በመምሬ አድባር ዛፍ ሥር ለዮሐንስ በዮርዳኖስ ተገልጸዋል ። ዘፍ 18+ 1-4, ማቴ 3+16

ሐ, የግብር ሦስትነት፦ የአብ ግብሩ መውለድ ማሥረጽ ፣ የወልድ ግብሩ መወለድ ፣ የመንፈስ ቅዱስ ግብሩ መሥረጽ ነው ። አብን ወላዲ ፣ ወልድን ተወላዲ፣ መንፈስ ቅዱስንም ሠራጺ ስላልን የሚበላለጡ አይደለም አንድ ናቸው ። እንዲህም ማለት ሦስት አማልክት ማለት አይደለም ። አንድ አምላክ ይባላሉ እንጂ
የአንድነታቸውስ ነገር እንደምን ነው ? ቢሉ በባሕርይ በህልውና በመለኮት በሥልጣን በፈቃድ አንድ ናቸው የህልውና አንድነታቸው በአብ ልቡናነት ወልድ መንፈስ ቅዱስም ያስቡበታል፤ በወልድ ቃልነት አብ መንፈስ ቅዱስም ይናገሩበታል ። በመንፈስ ቅዱስ እስትንፋስነት አብ ወልድም ህልዋን ናቸው ይተነፍሱበታል ።
ቅድስት ሥላሴ የሚል የሴት ቅጽል የተቀጸለላቸው ባሕርያቸውን አይቶ ነው ። ልጅ ከእናቱ ባሕርይ እንዲገኝ ይህም ዓለም ከሥላሴ ባሕርይ ተገኝቷልና ፤ እናት ለልጅዋ የሚያሻውን አስባ እንድታቀርብለት ሥላሴም ለፍጥረት ሁሉ የሚያስፈለገውን ሁሉ አስቀድመው ያዘጋጁለታል። ማቴ 6 +32 አንድም እናት ልጅዋ ቢያስቀይማት ፈጽማ እንዳትጥለው ሥላሴም ሰርቀው አመንዝረው ቢበድሏቸው ንስሐ ገብተው ቀኖና ይዘው ቢለምኗቸው ይቅር ይላሉና ። ማቴ 6 +32
ይህን የሥላሴ አንድነት ሦስትነት ካልተማሩ ሥርየተ ኃጢአት ተስፋ መንግሥተ ሰማያት አይገኝምና ፤ ይህንንም ምሥጢር ያፋለሰ ለየራሳቸው ልብ፣ ቃል፣ እስትንፋስ አላቸው ዘጠኝ አማልከት ናቸው ። እንዳለው እንደ ዮሐንስ ተዐቃቢ ፍዳን ይቀበላልና ፈጽሞ ጠንቅቆ መረዳት ይገባል ።
ሥላሴ የሚታየውንና የማይታየውን ሁሉ ካለ መኖር ወደ መኖር አምጥተው የፈጠሩ ድካም የማይሰማቸው በሞት የማይለወጡ ገዥ ፈጣሪ ናቸው ። ሥላሴ እንደዛሬ ሁሉ ዓለም ሳይፈጠር አስቀድሞ ባሕርያቸው ባሕርያቸውን ሲያመሰግን ይኖር ነበር ኋላ ግን ሰውና መላእክትን ስማቸውን ለመቀደስ ክብራቸውን ለመውረስ ፈጠሩ። ሌላውን ገን ለአንክሮ ለተዘክሮ ለምግበ ሥጋ ለምግበ ነፍስ ፈጥረውታል።

የበዓሉ ታሪክ

አብርሃም ቤቱን ከተመሳቀለ ጎዳና ሠርቶ የወጣ የወረደውን ያለፈ ያገደመውን እንግድነት ሲቀበል ይኖር ነበር ። ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ራሱን ገምሶ አጥንቱን ከስክሶ ከመንገድ ቆይቶ እንግዶቹን ወዴት ትሄዳለችሁ ? ይላቸዋል ። ርቦን ሊያበላን ጠምቶን ሊያጠጣን ከአብርሃም ዘንድ ይሉታል ፤ የወትሮው አብርሃም መሰላችሁን እኔም እንደ እናንተ ርቦኝ ያበላኛል ጠምቶኝ ያጠጣኛል ብዬ ብሄድ ራሴን ገምሶ አጥንቴን ከስክሶ ሰደደኝ ይላቸዋል ፤ እያዘኑ በመጡበት ይመለሳሉ ። እንዲህ አድርጎ 3 ቀን ሙሉ እንግዳ ከለከለበት እሱም ያለምስክር ግብር አላገባም ብሎ ሳይመገብ ቆይቷል ።

በሦስተኛው ቀን በቀትር ከድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ ሥላሴ በመምሬ አድባር ዛፍ ሥር ተቀምጠው ታዪት። ( ዘፍ 13 + 18 ) '' ገሀሡ አጋዕዝትየ ቤተ ገብርክሙ አብርሃም '' ጌቶቼ ከቤት ገብታችሁ እረፉ አላቸው ። ደክሞናልና እዘለን አሉት ። አንዱን አዝሎ ቢገባ ሁለቱ በግብር አምላካዊ ገብተው ተገኝተዋል ። እሱም ሦስት እንደሆኑ አውቆ ሣራን 3 መስፈሪያ ዱቄት ወስደሽ አንድ እንጎቻ አድርገሽ ጋግሪው አላት ፤ ጋግራ አቀረበች ፤ እርሱም ወይፈን አርዶላቸው ወተት እርጎ ጨምሮ አቅርቦላቸው ተመግበዋል / አቅረበ ሎሙ ሐሊበ ዕቋነ ወዕጉለ ላሕም / እንዲል ። መብላቸው ግን አሳት ቅቤ በላ እንደ ማለት ነው ። ይህንንም ሲያጠይቅ አርዶ አወራርዶ ያቀረበው ወይፈን ተነሥቶ '' ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ '' ብሎ አመስግኗል ። '' ድኅረ በላዕክሙ ላሕመ እንበይነ ፍቅረ ሰብእ ፍጹም ፤ ዘበኃይልክሙ ሐይወ ላሕም ፤ ሥላሴ ክቡራነ ስም '' እንዳለ ደራሲ።

በሚሄዱም ጊዜ ከሦስቱ አንዱ እግዚአብሔር ቃል አመ ከመ ዮም እገብእ ኀቤከ ፤ የዛሬ ዓመት እንደዛሬ ወዳንተ እመለሳለሁ ሚስትህ ሣራ ወንድ ልጅ ትወልዳለች ብሎ ለጊዜው ልደተ ይስሐቅን ፍጻሜው ግን ሰው ሆኖ የሚያድነው መሆኑን ነግሮታል ። ዘፍ 18 + 1- 14

ምንጭ ፦ መዝገበ ታሪክ 1 & 2
128 views20:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 13:19:50 አ/ተ/ሰ/ት/ቤት ትምህርት ክፍል pinned «ሰላም እንደምን አደራችሁ። የሰንበት ትምህርት ቤቱ ትምህርት ክፍል ከካልኣይ እስከ ራብዓይ ላሉ ተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር አዘጋጅቷል። ስለሆነም በመርሐግብሩ ላይ መካፈል የምትፈልጉ እኅቶች እና ወንድሞች ከሐምሌ 10/2014 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 22/2014 ዓ.ም ድረስ ባሉት እሑድ ቀናት ከምሽቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በመርሐግብሩ ላይ በመገኘት መንፈሳዊ ዕውቀት እንድትገበዩ እናሳስባለን።»
10:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 18:13:57 ለቀዳማይ የበጋ ተማሪዎች

ክርስቲያናዊ ሥነምግባር ትምህርት መምህሩ ስላልተመቻቸው የቀረ መሆኑን እናሳውቃለን ።
242 views15:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 09:45:16 ሰላም እንደምን አደራችሁ።

የሰንበት ትምህርት ቤቱ ትምህርት ክፍል ከካልኣይ እስከ ራብዓይ ላሉ ተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር አዘጋጅቷል። ስለሆነም በመርሐግብሩ ላይ መካፈል የምትፈልጉ እኅቶች እና ወንድሞች ከሐምሌ 10/2014 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 22/2014 ዓ.ም ድረስ ባሉት እሑድ ቀናት ከምሽቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በመርሐግብሩ ላይ በመገኘት መንፈሳዊ ዕውቀት እንድትገበዩ እናሳስባለን።
388 viewsedited  06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-20 19:21:25 ለቀዳማይ ተማሪዎች
እሑድ ጠዋት ትምህርት ባለመማራቹ ምክንያት ሰኞ 12 :00 ሰዓት ማካካሻ ይሰጣል የተባለ ቢሆንም በዝናቡ ምክንያት ትምህርቱ ሳይሰጥ ቀርቷል ስለዚህ ነገ ማግሰኞ 12 : 00 ትምህርቱ ይሰጣል ።

ላልሰሙ ጓደኞቻቹ አሳውቁ
511 viewsedited  16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 16:52:14 ለቀዳማይ ተማሪዎች በሙሉ ( የበጋ ተማሪዎች )
በ12 -10 -2014 ዓ.ም. ጠዋት የነበረው የትምህርት መርሐ ግብር አልተካሄደም ስለሆነም ለዛሬው ማካካሻ ስለምትማሩ ነገ ሰኞ 12 : 00 አቡነ ኢየሱስ ሞዓ ቤተ-መጻሕፍት እንድትገኙ እናሳስባለን ::

ላልሰሙ ጓደኞቻቹ አሳውቁ
675 views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 22:14:56 ከካልኣይ እስከ ራብዓይ ላላችሁ ተማሪዎች

የሰንበት ትምህርቱ ቤት ትምህርት ክፍል ከካልኣይ እስከ ራብዓይ ላላችሁ ተማሪዎች ለአንድ ወር ተምሮ የማስተማር ሥልጠና ትምህርት ክፍሉ ለመስጠት ዝግጅቱን የጨረሰ ሲሆን በዚህ ሥልጠና መሳተፍ የምትፈልጉ ወንድሞች ካላችሁ አቡነ ኢየሱስ ቤተ-መጻሕፍት እየመጣችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን ።

የሰንበት ትምህርት ቤቱ ትምህርት ክፍል
665 viewsedited  19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 22:14:56 ማስታወቂያ
ከካልኣይ እስከ ራብዓይ ላሉ ተማሪዎች
የሰንበት ትምህርቱ ቤት ትምህርት ክፍል ከካልኣይ እስከ ራብዓይ ላላችሁ እንዲሁም ከዚህ ቀደም ሣልሳይ ጨርሳችሁ አሁን በመማር ላይ ያልሆናችሁ ወጣት አባላትን የሚያካትት ጥያቄና መልስ ውድድር አዘጋጅቷል ። ስለሆነም በዚህ ውድድር መሳተፍ የምትፈልጉ ሁላችሁ አቡነ ኢየሱስ ቤተ-መጻሕፍት መጥታችሁ እንድትመዘገቡ እናሳስባለን ። ( ስለውድድሩ የበለጠ መረጃ ከፈለጉ ትምህርት ክፍሉን ያነጋግሩ )

የሰንበት ትምህርት ቤቱ ትምህርት ክፍል
604 views19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ