Get Mystery Box with random crypto!

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 10ኛ ሳምንትና የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ! ቤትኪንግ የኢትዮ | Amhara Sport

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 10ኛ ሳምንትና የዲሲፕሊን ውሳኔዎቹ!

ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 12ኛ ሳምንት በተደረጉ ሰባት ጨዋታዎች ሁለት ጨዋታዎች በመሸናነፍ አምስት ጨዋታ በአቻ ሲጠናቀቁ 8 ጎሎች በ14 ተጫዋች ተቆጥረዋል። የጎሎቹ አገባብ አንድ በፍፁም ቅጣት ምት ቀሪዎቹ በጨዋታ የተቆጠሩ ናቸው። በሳምንቱ 25 ተጫዋቾችና የቡድን አመራሮች በቢጫ ካርድ ሲገሰፁ አንድ ተጫዋች በቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ ወጥቷል።

የኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር አመራርና ስነ-ስርዓት ኮሚቴ አርብ ታህሳስ 7 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የተደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያ(ዎች)ከዳኞች እና ከታዛቢዎች የቀረቡለትን የዲሲፕሊን ሪፖርት ከመረመረ በኋላ የተለያዩ ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

በተጫዋቾች ምንይሉ ወንድሙ(መቻል) በ12ኛ ሳምንት ጨዋታ ከጨዋታ በኋላ ዳኛን አፀያፊ ስድብ በመሳድብ በቀይ ካርድ ከጨዋታ ሜዳ የተወገደ ስለመሆኑ ሪፖርት የቀርበበት ለፈፀመው ጥፋት በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 3 ጨዋታ እንዲታገድ ና በተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት ብር 3000 /ሶስት ሺ/ እንዲከፍል ተወስኗል።

ባህርዳር ከተማ ክለቡ ከሲዳማ ቡና ጋር ባደረገው ጨዋታ የባህርዳር ከተማ ቡድን አምስት በተለያዩ ጥፋቶች ካርድ የተሰጣቸው በመሆኑ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት የገንዘብ ቅጣት ብር 5000 /አምስት ሺ/ እንዲከፍል ተወስኗል፡፡

በክለቦች ባህር ዳር ከተማ ከሲዳማ ቡና ጋር በነበረው የ 12ኛ ሳምንት ጨዋታ የባህር ዳር ከተማ ደጋፊዎች የዕለቱን ዋና ዳኛ አፀያፊ ስደብ ስለመሳደባቸው ሪፖርት በመቅረቡ ደጋፊዎቹ በዕለቱና ከዚህ በፊት ተሳድበው በተቀጡት ቅጣት ሊታረሙ ባለመቻላቸው ክለቡ በኢ.እ.ፌ ዲሲፕሊን መመሪያ መሰረት 75, 000 ብር እንዲከፍል ተወስኗል።

@amharasport