የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ የ2015 የውድድር ዘመን የእጣ ማውጣት ላይ በክፍያ አለማጠናቀቅ ምክንያት እጣ ውስጥ ሳይገቡ መቅረታቸው የሚታወስ ሲሆን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ክፍያ ያጠናቀቁ ክለቦች በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፅሕፈት ቤት በተደረገ የእጣ ማውጣት የምድብ ድልድል ውስጥ ተካተዋል። ውድድሩ በመጪው ህዳር 20 በአራት ከተሞች መካሄድ የሚጀምር ሲሆን ክለቦች ውድድር በሚያደርጉበት ከተማ ህዳር 19/2015 የቅድመ ውድድር ስብሰባ የሚከናወን ይሆናል። 48 ክለቦች የሚሳተፉበት የ2015 የኢትዮጵያ አንደኛ ሊግ ምድብ ድልድል እና ውድድር የሚያደርጉበት ከተማ በምስሉ ላይ ተጠቅሷል። (EFF) @mandurasport 2.6K views13:17