Get Mystery Box with random crypto!

Abissiniya Empire #አማራ

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharaa — Abissiniya Empire #አማራ A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharaa — Abissiniya Empire #አማራ
የሰርጥ አድራሻ: @amharaa
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.69K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ Abissiniya Empire #አማራ የተሰኘ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።⬇️ለፈጣንና አዳዲስ መረጃዎች

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 19:48:39
አሁናዊ መረጃ ከስፍራው!

በወልቃይት በረከት እና ሉግዲ መሃከል ትናንት በረድ ብሎ የነበረው ጦርነት ዛሬ ሌሊት 9 ሰዓት በድጋሚ ጀምሮ  እስከ ረፋዱ 3 ሰዓት ድረስ በከባድ መሳሪያ የታገዝ ጦርነት ተካሂዷል።

የትህነግ ጦር አስቀድሞ ከሰራቸው 5 ባለ ሶስት ደረጃ  ምሽጎች ውስጥ ሶስቱ ተሰብረዋል። የተቀሩትም በቀጣይ 24 ሰዓታት ውስጥ እንደሚሰበሩ አሁን ያለው ጦርነት ምስክር ነው። መከላከያ ሰራዊቱ እና ልዮ ኃይሉ በጥምር እያጠቁ ነው። ከሁመራ ከተማ 25 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ነው ጦርነቱ በማይካድራ አቅጣጫ እየተካሄደ ያለው።

ፋኖ፣ሚሊሻውና የአካባቢው ታጣቂ በቅርብ እርቀት ላይ ቢሰፍርም እስካሁን እንዲገባ አልተፈቀደም። ማይካድራን ጨምሮ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ከተማ ሁመራ በፋፁም መረጋጋት እና ሰላም ትገኛለች።
291 views16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 18:46:00
ሰበር መረጃ!
*
በማዕከላዊ እዝ የሚመራው የሰቆጣ ግንባር ጥምር ጦር ለአመታት የገነቡትን ምሽግ እየሰባበረ ለመቀሌ ከ50 ኪሜ ያልበለጠ ርቀት ያላችን ከአበርገሌን ከተማ አለፍ ብላ የምትገኘውን #የዛካ ከተማን ተቆጣጥሯል።
438 views15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 13:44:56
የወልቃይት ጠገዴ ጀግኖች አሸባሪውን ለመፋለም በዚህ መልኩ አሸኛኘት ተደርጎላቸዋል!
659 views10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 11:55:05
መረጃ!

ከሱዳን አቅጣጫ በበረከት ወልቃይት በኩል ወደ ኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ጦርነት ከከፈቱት የህወሓት ታጣቂዎች በተጨማሪ የኤርትራን መንግሥት በትጥቅ ትግል ለመጣል በህወሓት ከፍተኛ ድጋፍ የሚደረግላቸው በቁጥር ጥቂት የኤርትራ ታጣቂዎች ጭምር እንዳሉበት የሁመራ መረጃ ምንጮቻችን ጠቁመዋል።
700 views08:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 11:33:27
#ራያ ሸለቆዎች ውስጥ የመሸገው የህወሓት ኃይል!

ወራሪው ሃይል ተጠቅሎ የራያ ሸለቆ ውስጥ ገብቷል። በጎሊና እና አላ ውሃ ወንዞች የአማራና አፋር ክልል አዋሳኝ አከባቢዎች ከጎብየ በደቡብ በኩል እስከ ዲቢ መገናኛ ቆላ መውረጃ በሰፊው  ተሰግስጓል። ቁጥሩ ከ30-50ሺህ የሚገመት ሃይል በዚህ ሸለቆ ውስጥ ገብቷል። የያዟቸው መሳሪያዎች ብሬይን፣ ዲሽቃ፣ መትረየስ፣ ስናይፐር፣  ከሶስት የማይበልጡ ዙ-23 እና አንድ መድፍ ይዟል።

በጎሊና እና አላ ውሃ ወንዞች መሃል የመሸገውና የወርቈን ተራሮች አጥሮ የተቀመጠው ይሄ ሃይል የጉዞው አላማ ምንድነው? ትጥቁን በግመልና አህያ ጭኖ በራያ ጨርጨር ዞብል ተራራ አድርጎ በራማ-ቦረን-ጋቲራ-ዲቃሎን  አድርጎ እጅግ በጣም ብዙው ሃይል ወርቄ ገብቷል። ሌላኛው ሃይል ቦረን ተነስቶ አረቁቴ ወርዶ  ገደመዩ ነዲ ተራራን ተገን አድርጎ ወደ ዲቢና አጋምሳ መንደሮች ወርቄ ገብቷል።

ይሄ ሁሉ ሃይል አላማው ሚሌ ነው!! መንገዱ ግን ተራራማውና ቆላማው የወሎ ክፍል ነው። ወራሪው ሃይል ገላጣና በርሃማ መስመሮችን ረዥም ርቀት መጓዝ የቱን ያክል አክሳሪና አዋራጅ መሆኑን ከባለፈው ውርደቱ ተምሯል። ስለሆነም  ሰሜን ወሎ የግዳንና ዋግ ትግል ጠንክሮ ወራሪውን ሃይል ልቡንና አቅሙን ካልከፈለው የሚከተሉት መስመሮች በከባድ ጥንቃቄ ይፈልጋሉ፥

1)  በወርቄ አላ ውሃ ወንዝን ተሻግሮ ሃሮን ታኮ ወደ ድሬ ሮቃ ሰዶማና ቢስቲማ መስመሮችን በዋናነት ያልማል።

2) በወርቄ ምስራቅ በኩል ወርዶ በኡዋ በላይ ማለፍም ያስብ ይሆናል። በመሆኑም አሁን እየተደረገ ያለውን ትግል በሚገባ በመቆስቆስ ወርሪው ከገባበት የራያ ሸለቆ እንዳይወጣ ማድረግ ያስፈልጋል።

መረጃው የያሲን መሀመድ አሊ ነው!
699 views08:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 10:57:08
አሁናዊ መረጃ!

የትግራይ ወራሪ ሀይል በሰሜን ጎንደር ዞን አዲአርቃይ ወረዳ በር ማሪያም በሚባለው አቅጣጫ በዚህ ቅፅበት ተኩስ የከፈተ ሲሆን የወገን ጦርም ወረራውን ለመመከት ውጊያ ጀምሯል። የዛሬውን ጨምሮ አሸባሪው ቡድን  አማራ ክልልን ለመቆጣጠር በአራት ዞኖች ማለትም ሰሜን ወሎ ዞ፤ዋግኽምራ ብሄረሰብ ዞን፤ሰቲት ሁመራ ዞን እና በሰሜን ጎንደር የዞን አሰተዳደር ሰር በሚገኙ ወረዳዎች ውሰጥ ግንባር ፈጥሮ እየተዋጋ ይገኛል።

አሸባሪው ቡድን የአማራ ክልልን አስተዳደራዊ ወሰን በሀይል ጥሶ ለመግባት ጦርነት ከመክፈቱ በተጨማሪ እድል ቀንቶት በተቆጣጠረው አካባቢ የሚገኙ ህዝቦችን እየገደለ፤ንብረት እየዘረፈ፤ሀብት እያወደመ ነው። ይሁን እንጅ አቅሙ በፈቀደው መጠን የአማራን ህዝብ ለማጥፋት እየጣረ መሆኑ ግልፅ ሆኖ ሳለ ከህዝቡ ከባድ አፀፋ ሲገጥመው ፀባችን ከብልፅግና መንግስት ጋር እንጅ ከአማራ ጋር አይደለም የሚል የተለመደ ማደናገሪያ ፕሮፓጋንዳውን መንዛት ጀምሯል።
673 views07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 22:08:34
#ወለጋ!

በኦሮሚያ ክልል ሆሮጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ አገምሳ ከተማ ትናንት ከማለዳ ጀምሮ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ 55 ሰዎች መገደላቸው ተዘገበ። የአከባቢው ነዋሪዎች ለዶይቼ ቬለ እንደተናገሩት ለአንድ ዓመት ያህል የመንግስት የፀጥታ ኃይሎች የአከባቢውን ፀጥታ ሲያስከብሩ ነበር።

ይሁንና ባለፈው ዕሁድ ነሐሴ 22 ቀን፣ 2014 የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ከከተማዋ መነሳታቸውን ተከትሎ የተለያዩ ስያሜ ያላቸው ታጣቂዎች በከተማዋ መፈራረቃቸውን ነው የዐይን እማኞች የገለጹት። የአይን እማኞቹ ለዶይቼ ቬለ እንዳሉት «መንግስት ‘ሸነ’ ያላቸው “የኦሮሞ ነጻነት ጦር” ሰኞ ጠዋቱን ገብተው ከተማዋን ተቆጣጠሩዋት» ብለዋል። የዐይን እማኙ አክለውም እንዳብራሩት ታጣቂዎቹ ከተማዋ ውስጥ ሙሉ በሙሉ መንቀሳቀስ ከጀመሩ በኋላ ወደ 59 መሳሪያ ከማህበረሰቡ አስፈትተው በዚያው ሰኞ ቀን ከተማዋን ለቀው ቢወጡም ተመልሰው በመምጣት ከ55 በላይ ሰዎችን ገለው ሄደዋል ብሏል፡፡ 

ዘገባው  የጀርመን ድምፅ ራዲዮ ነው!
829 views19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:38:44
“አማራ ሕዝብ ቁርጠኛ መሪ ካልፈጠረ እንደቆሰለ ይኖራል።” -ብ/ጄ ተፈራ ማሞ
840 views17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 16:40:56
የምስራቅ አማራ ፋኖን እናግዝ!

"…ሜዳውም ፈረሱም ይኸው…!!
ለሁሉም ሀገር ወዳድ እና አማራ ሼር አርጉላቸው!!

"…አርበኛ ፋኖ ዋርካው ምሬ ወዳጆ የሰጠኝ፣ ያዝማ ዘመዴ፣ ጻፍ ብሎ ራሱ በቃሉ የነገረኝ፣ ኋላም ከአርበኛ ፋኖ አቤ ጋር አገናኝቶኝ ያረጋገጠልኝ፣ እኔም የባንክ አካውንቱን ኮፒ ፎቶ አንሥታችሁ ላኩልኝ ብዬው የላከልኝ የምሥራቅ ዐማራ ፋኖ የሀብት ማሰባሰቢያ፣ የኮቾሮና በዝናብ ጊዜ የላስቲ መግዣ የባንክ አካውንታቸው ይኸው። እደግመዋለሁ ሜዳውም፣ ፈረሱም ይኸው።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የባንክ ሂሳብ ቁጥር
1000485333146
ምሬ ወዳጆ (የምሥራቅ ዐማራ ፋኖ ዋና አዛዥ) ከድር ሰይድ (ምክትል አዛዥ) እና
መሰረት ጫኔ (ሃብት አፈላላጊ)

"…የኮቾሮ መግዢያውን በዚህ ላኩላቸው። የተሰደዳችሁ ወጣቶች ተመለሱ። ሴቶችም በቀያችሁ ሆናችሁ ስንቅ አቀብሉ። ርስታችሁን ጥላችሁ አትሰደዱ። ሞትም ሰርግ በቀዬ ነው የሚያምረው። ስደት አዋራጅ ነው። ሁሉ ነገር በቀዬ ነው የሚያምረው። ተመለሱ። ጦርነቱ ካልደረሰበት ሥፍራ ተሰዳችሁ የመጣችሁ ተመለሱ። "…በሉ ጀምሩ…!!

መምህር ዘመድኩን በቀለ
920 views13:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 13:08:15
ማይካድራ ላይ በሺዎች የጨረሰብን ህወሃትን ለመበቀል ጊዜው አሁን ነው። በሰላሙ ጊዜ አራሽ በችግር ጊዜ ተኳሽ የሆነው የሁመራ ገበሬ ትጥቁን ሸካክፎ ወደ ግንባር እየተመመ ይገኛል።
886 views10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ