ሰበር ዜና
በጎንደር ህዝብ ላይ በሞርተር እና በዲሽቃ የታገዘ ጦርነት በኦህዴድ ሠራዊት ተከፈተ
ሻለቃ አርበኛ መሳፍንትን ከ1 ሺህ በላይ የኦህዴድ ሠራዊት አጅሬ ጃኖራ በራ የምትባል ቦታ ላይ በመክበብ በሞርተር እና በዲሽቃ ተኩስ ከፍተውበታል ሲል የመረጃ ምንጫን አድርሶናል።
አርበኛ መሳፈንትን እንይዛለን በሚል ዛሬ ከነገ በቡድን መሳሪያ ጦርነት የከፈተው የኦህዴድ ሠራዊት በህፃናት፣ሴቶች እና ሌሎች ንፁሃን አማሮች ላይ ጭፍጨፋ እየፈፀመ ነው ተብሏል።
የጎንደር ህዝብ ወደ ስፍራው በማቅናት መንገድ እንዲዘጋ፣መረጃ እና ስንቅ በአስቸኳይ እንዲያቀርብ ጥሪ ቀርቧል።
በሃገር ውስጥም ይሁን በመላው ዓለም የሚገኝ ማንኛውም አካል እንዳሁም የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኦህዴድ/ብልፅግና በአማራ ህዝብ ላይ በይፍ ጦርነት መክፈቱን እንዲያውቅልን ሲሉ ገልፀዋል።
በሸዋ፣በወሎ እና በጎጃም የሚገኝ ማንኛውም አማራ በጎንደር ህዝብ ላይ ኦህዴድ በይፋ ጦርነት አውጆ ህፃናትን እየገደለ መሆኑን አውቆ ዛሬውኑ ለትግል እንዲነሳ ጥሪ ቀርቧል።