2021-10-26 18:12:22
ለበጎ ነው!!
አንድ ሰው በባህር ብቻውን በጀልባ እየተጓዘ በማዕበል ተመታና ጀልባው ተሰባብራ በባህሩ ውስጥ ሰጠመች። ሰውዬው እንደምንም እራሱን አድኖ አንድ ደሴት ላይ ያርፍና ጎጆ ነገር ሰርቶ ለቀናት ለብቻው እዛች ደሴት ላይ ይኖራል።
ምግቡን ዓሳ አያጠመደ እየተመገበ
ብዙ ቆየ።
አንድ ቀን ለምግብ የሚሆነው አሳ ሊያጠምድ ባህሩ ዳርቻ ላይ መንጠቆውን ይዞ ለረጅም ሰአት እየጠበቀ እያለ በድንገት ጭስ ሸተተው። ዞር ብሎ ሲያይ ያቺ ጎጆው እየነደደች ነው። እየሮጠ ቢመለስም ጎጆዋን ሊያድናት አልቻለም።
ለካ ዓሳ ለማብሰል ያቀጣጠለው እሳት ተያይዞ ጎጆውን አንድዷታል አለቀሰ፤ ፈጠሪውን ወቀሰ፤ እንዴት እዚህ ባህር ላይ ብቻዬን ጥለኸኝ ከቤተሰቦቼ ነጥለኸኝ ስታበቃ በስንት ልፋት የሰራኋትን ጎጆ ታቃጥልብኛለህ ብሎ አለቀሰ፤ አማረረ።
ከደቂቃዎች በኃላ አንድ ድምፅ ሰማ፤ ወደ ድምፁ ፊቱን ሲያዞር አንድ ትልቅ መርከብ አየ፤ ተደሰተ። የመርከቡ ሰዎች መጥተው ጭነው ወሰዱት። ከዚያም ለመርከቡ ሰዎች ጠየቃቸው! እንዴት አገኛቹኝ?
እዚህ አካባቢ እዚህ ባህር ላይ ማንም አይመጣም እኮ እናንተ እንዴት አገኛቹኝ?
አላቸው። መርከበኞቹም "እኛማ በዛኛው በኩል ዞረን እየሄድን ነበር። ከዚህ በኩል ጭስ አየንና እዚህ ሰዉ ይኖራል ብለን መጣን፤" አንተ አገኘን አሉት።
አቤት ጌታዬ ለካ ከዚህ ከስቃዬ ልታውጣኝ ፈልገህ ነው ትንሿ ጎጆዬን ያፍርስከው፤ ወደ ትልቁ ቤት ልትውሰደኝ ነው አለ።
አንዳንዴ የሆነ ነገር ስናጣና ሲበላሽብን ሰውንም ፈጣሪንም ስናማርር እንኖራለን። ግን ካጣነው እና ከጎደለብን ነገር ጀርባ ብዙ ጥሩ ነገር ልናገኝ እንደምንችል እንዘነጋለን። በችግራችን ጊዜ መጠጋት ያለብንን ፈጣሪያችን እንረሳዋለን። ከዚያም አልፈን የሁሉ ነገር ፈጣሪ የሆነውን አምላክ እንወቅሳለን።
ወዳጄ ሆይ ሁሌም ቢሆን በማንኛውም መጥፎ አጋጣሚ ውስጥ ሁነንም መልካም ነገሮችን ማሰብና በፈጠረን አምላክ ተስፋ ማድረግን ልማድ እናድርገው፡፡
313 views15:12