Get Mystery Box with random crypto!

ጥር 12 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለከፍተኛ የመንግስት ሃ | Ahmed Habib Alzarkawi

ጥር 12 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለከፍተኛ የመንግስት ሃላፊነት ቦታዎች ሹመቶች ሠጡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 74(2) መሰረት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ የሚከተሉትን ሹመቶች እንዲያጸድቅ ጠይቀዋል፦

1. ዶ/ር አለሙ ስሜ - የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር
2. ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ - የማዕድን ሚኒስትር
3. ዶ/ር ግርማ አመንቴ - የግብርና ሚኒስትር

በተጨማሪም ከጥር 10፣ 2015 ጀምሮ የሚከተሉትን ሹመቶች ሰተዋል፦

1. አቶ ማሞ ምሕረቱ - የብሔራዊ ባንክ ገዢ
2. ወ/ሮ አለምፀሐይ ጳውሎስ - የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር
3. ዲያቆን ዳንኤል ክብረት - የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማኅበራዊ ዘርፍ
አማካሪ ሚኒስትር
4. አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ - የጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጭ ፖሊሲ
አማካሪ ሚኒስትር
5. አቶ መለሰ አለሙ - በሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት
ግንባታ ማስተባበሪያ የዘርፍ አስተባባሪ

//

#PMOEthiopia