Get Mystery Box with random crypto!

ያሙፍረደል ዓለም ሙሀመድﷺ ቻናል

የቴሌግራም ቻናል አርማ allahbel — ያሙፍረደል ዓለም ሙሀመድﷺ ቻናል
የቴሌግራም ቻናል አርማ allahbel — ያሙፍረደል ዓለም ሙሀመድﷺ ቻናል
የሰርጥ አድራሻ: @allahbel
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 135
የሰርጥ መግለጫ

አስታየት ሀሳብ ካለዎት
@RAYJ4
Join us and share
t.me/allahbel

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-01 06:58:09
ሁል ጊዜ በሐሳብህ ሀቀኛ ሁን !

Armala Charity
@Armala_charity2
21 views ⓵, 03:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 21:51:22 #በ ጁመአው ለይል ሹክ ልበላችሁ

አዘጋጅና ፀሀፊ ፦ ካሊድ (kalido ye umi)

ሁሌም በልባችን ውስጥ ኖት!

#የመሰናበቻው_ሐጅ

<<ሙዓዝ ሆይ፡ ከዚህ አመት በኋላ ላታገኘኝ ትችላለህ። ምንአልባትም በዚህ መስጂድና በቀብሬ አጠገብ ታልፍ ይሆናል።>>

የጥሪው ተግባር፣ መልእክት የማድረሱ ስራ፣በአላህ ብቸኛ አምላክነት እና በነብዩ ሙሐመድ ﷺ መልእክተኛነት መሰረት ላይ አዲስ ሕብረተሰብ የማነፁ እንቅስቃሴ ከተጠናቀቀ በኋላ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ምድራዊ ህይወታቸው ወደ መጨረሻው መቃረቡን የሚገልጽ አንዳች ሚስጥራዊ መልእክት ከልቦናቸው ውስጥ ሰፈረ። እናም በ 10ኛው ዓመተ ሂጅራ ሙዓዝን ወደ የመን ሲልኩ እንዲህ ነበር ያሉት።

ሙዓዝም ያንን ሲሰማ ከእርሳቸው የመለየቱ ነገር ታሰበውና ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ።

በዙሪያቸው 124 ሺህ ወይም 144 ሺህ ሰዎች በተሰበሰቡበት ከመሀከላቸው ተነሱና የሚከተለውን ሁለንተናዊ ንግግር ከዓረፋ ጋራ ላይ ሆኖ ረቢአህ ቢን ኡመያህ ቢን አልኸለፍ በማስተጋባት አሰሙ።

<< ሰዎች ሆይ ንግግሬን ስሙ። ምን አልባትም ከዚህ አመት በኋላ በዚህ ቦታ ላይ ዳግም ላላገኛችሁ እችላለሁ። ይህ ቀናችሁ በዚህ ወራችሁ እና በዚህ ሃገራችሁ ላይ የተከበረ እና እርም እንደሆነ ሁሉ ደማችሁም እና ገንዘባችሁም በእናንተ ላይ እርም ነው። #አዋጅ የመሐይምነት ዘመን ድርጊቶች ሁሉ ከእግሮቼ ስር ውድቅ ሆነዋል። የቅድመ ኢስላም(የጃሂልያ) የደም ብቀላ ሁሉ ውድቅ ሆኗል። ከደሞቻችን መካከል መጀመሪያ ውድቅ የተደረገው የቢን ረቢእሀ ቢን ሐሪስ ደም ነው። የመሐይምነት ዘመን አራጣ ውድቅ ነው። ከአራጣዎቻችን መካከል በመጀመሪያ ውድቅ የተደረገው የአባስ ቢን አብድልሙጦሊብ አራጣ ነው። እርሱ ሙሉ በሙሉ ውድቅ ሆኗል።

በሴቶች ጉዳይ አላህን ፍሩ። ምክንያቱም በአላህ አደራ ያዛችኋቸው። በአላህ ቃል ብልቶቻቸውን የተፈቀዱ አደረጋችሁ። እናንተ በእነርሱ ላይ ያላችሁ መብት የማትፈልጉት ሰው ፍራሻችሁን እንዳይረግጥ ሊያደርጉ ሲሆን ፣ይህን ካልፈፀሙ ለስሙ ያህል መታ አድርጓቸው። እነርሱ በእናንተ ላይ ያላቸው መብት ደግሞ ቀለባቸውንና አልባሳቶቻቸውን ተገቢ በሆነ ሁኔታ ልታመቻቹላቸው ነው።

የአላህን መፅሐፍ ትቼላችኋለሁ። በርሱ ከተመራችሁ መንገድ አትስቱም። ሰዎች ሆይ፣ ከኔ በኋላ ነብይ የለም። ከእናንተ በኋላም ኡማም የለም። #አዋጅ ፣የጌታችሁን ጀነት ትገቡ ዘንድ ጌታችሁን አምልኩ። አምስት ወቅት ሰላታችሁን ስገዱ። የረመዷን ወር ፆማችሁን ፁሙ። የገንዘባችሁን ዘካ፣ ወዳችሁና ፈቅዳችሁ አድርሱ። የአምላካችሁን ቤት ሐጅ አድርጉ። መሪዎቻችሁንም ታዘዙ።

ይህን ከተናገሩ በኋላ እንዲህ ሲሉ ጠየቁ?

<ስለእኔ ብትጠየቁ ምን ትላላችሁ?>

ሰዎችም < እርስዎ መልእክቱን በታማኝነት እንዳደረሱን እንመሰክራለን።> አሉ።

{ፊዳከ ነፍሲ ኡሚ ወ አቢ ያረሱለላህ}

ሳምንት በአላህ ፍቃድ በሌላ ፅሁፍ እመለሳለሁ !

መልካም የጁመዓ ለይል (ኸሚስ) ውዶቼ

join @mahbubil
21 views ⓵, 18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 23:44:42 እዉነተኛ ታሪክ
  #አስለቃሽ #የቴሌግራም
              #ፕሮፋይል

      #Part

    እኔም እናት እና አባቴ በዚህ ጉዳይ ሲጣሉ ሲቸካቸኩ አባቴ አይሆንም እያለ ሲጮህ ይህ ችክችክ ወደ ሌላ ወደ ቤተሰብ ፀብ እንዳይዞር እኔዉ እራሴ መፍታት ማስታረቅ አለብኝ ብየ ወሰንኩ ግን አባቴን ማሳመኑ አደራዉ እኔ ጋር እንደሆነ ተገነዘብኩኝ ...በራስ መተማመን ይዤ አባቴ የተናገረኝን ቢናገረኝ ላልቀየም ላላለቅስ የአላህ ቀድር ከሆነ በእኔ ምንም መለወጥ አልችልም ብየ አስቤ.. እራሴን አሳምኜ በሩን ስከፍተዉ እናት እና አባቴ መቸካቸካቸዉን አቁመዉ ሁለቱም ወደ እኔ ትኩረታቸዉን አደረጉ፡፡

ቤቱ ፀጥ አለ ማን ወሬ እንደሚጀምር አስፈራኝ ግን እኔ መጀመር እንዳለብኝ ተረዳሁ ...ወደ አባቴ ጎን ሂጄ ቁጭ አልኩኝ
    አባቴ ምነዉ እናቴ ጋር አለመግባባት ምን ተፈጠረ??? አልኩት ነገሮችን እንዳልሰማሁ ሁኜ
.....እሱም የምሰማዉ ነገር እዉነት ነዉ እንዴ??? አለኝ
.....እኔም እዉነት ቢሆን ለአንተ ደስ አይልህም እንዴ?? አልኩት
.....እሱም የጠየኩልሽን አጭር መልስ ንገሪኝ ከአፍሽ ልስማዉ አለኝ
...እኔም ከእኔ መነገሩ ጥቅም የለዉም እናቴም ነግረሀለች አዎ እዉነት ባቢ ዙበይርን ነገ እናንተን ላስተዋዉቅ ምሳ ጠርተነዋል ከነ እህቱ አልኩት
....አባቴም እኔ አባትሽ አይደለሁ?? እስከ አሁን እንዴት ሳትነግሪኝ እኔ የልጄን ሂወት መወሰን አልችልም ማለት ነዉ?? ቢሆንም ባይሆን እንዴት አንድ ቀን ሲቀረዉ ትነግሪኛለሽ ?? እኔ ከእናተ እርቄ የመንግስት መስሪያ ቤት የምሰራዉ አስተካክየ ቁርስ በልቼ ምሳ በቅጡ የማልበላዉ ለማን ብየ መሰለሽ ለአንድ ፍሬ ልጄ ለአንቺ ብየ እኮ ነዉ፡፡ በጣም ጥፋተኞች ናችሁ አዝናለሁ አለኝ፡፡
 አባቴ እዉነቱን ነዉ የቤተሰብ ፍቅር እርቆ  በአገኘዉ የወር ደመወዝ ነዉ የሚያስተዳድረን ግን ዙበይር ጋር እዚህ ደረጃ ለትዳር እንደርሳለን ብየ ትዝም ብሎኝ አያቅም..... ደግሞ ቀድሜ ብነግራቸዉ ይሆናል ብየ ባይሳካ ቤተሰቦቼ እኔን ምን ይጠረጥሩኛል ?? አጃጅሎ ተዋት ብለዉ ወይ እኔን አያምኑኝም ወይ እሱ ጋር ፀብ እንደሚኖር መዘንጋት የለብኝም፡፡
   አሁን ያለኝ አማራጭ አባቴ ያለኝን የጠየቀኝን ከመመለስ እኔ ይቅርታ ብለዉ የተሻለ መሰለኝ፡፡

ከአባቴ ጎን ተነስቼ  ከእግሩ ስር ተደፍቼ አባቴ ጥፋተኛ ነኝ ይቅር በለኝ እኔ እንደዚህ ይከፋሀል ብየ ትዝም አላለኝ ሰርፕራይዝ ላረግህ ነበር ሀሳቤ ይቅር በለኝ እኔ ይሄ ትዳር ይሆናል ብየ አላሰብኩትም ፡፡ ለእናቴ እንኳ የነገርኳት ከሶስት ቀን በፊት ነዉ እኔ ዙበይር የሂወት አጋሬ ይሆናል ብየ አስቤዉም አላቅ አዉፍ በለኝ ብየ አለቀስኩኝ አባቴ እግር ላይ ተደፍቼ፡፡
    አረ ልጄዋ አታልቅሺ እኔ የአንቺን ለቅሶ አልፈልግም ሀገር ለሀገር የምዞረዉ አንቺ ደስተኛ እንድትሆኝ ነዉ አዉፍ ብየሻለሁ ብሎ ግንባሬን ሳመኝ
.....እኔም በደስታ እሺ የነገዉን ምሳ ፕሮግራም እዚሁ ልትገኝ ተስማማህ?? አልኩት
   አንዴ ጥያቄ ልጠይቅሽ ??አለኝ
..... ስለዙበይር ብዙ ነገር ጠየቀኝ መለስኩለት የጓደኛየ ወንድምም እንደሆነ..እናቴ እንደጠየቀችኝ
..... ሀብቱን አይተሽ እንዳይሆን አለኝ፡፡ እኔም በጭራሽ ይሄ እንዳለዉ ያወኩት ቅርብ ቀን ነዉ እኔ መስፈርቴ ብር አይደለም ነበር እኔ ማንነቴን አዉቆ ስለተቀበለ ነዉ የመረጥኩት አልኩት
    አባቴም ግን ልጄ እኔ የጠየቁኝ አሉ እሺ ከህመሟ ይሻላት እያልኩ መልሻለሁ  የነገዉን ምሳ ችግር የለም እንተዋወቃለን ፡፡ ግን ብትረጋጊ እና እኔ የጠየቁኝን ሰዎች አጥንተሽ ለምን መርጠሽ አታገቢም??? አለኝ
......እኔም ሳቅ እያልኩ አባቴ የመጡልኝ እኮ ማንነታቸዉን አላዉቅም ፀባያቸዉን ከኔ ምን እንደሚፈልጉ የማቀዉ የለኝም ዙበይር እኮ ከኔ የሚፈልገዉ ፍቅሩን እና የትዳር አጋሩ እንድሆን ነዉ፡፡ አንተን የጠየቁህ ለክብራቸዉ ለዘራቸዉ ሊጨነቁ ይችላሉ ደግሞ መቀራረብ እንጠናና በሚለዉ እኔም የእሱን ፀባይ ልወቅ ስል እሱም የኔን ፀባይ ልወቅ ሲል መቀራረብ አላህ ብዙ የከለከሉ ወንጀሎችን ልንሰራ እንችላለን ፡፡አንተ አስተዋወከን  ቀርባችሁ ተዋወቁ ነዉ የምትለን ..ቀርባችሁ ተዋወቁ  ማለት ከዚህ የባሰ ምን ይፈጠራል?? አባቴ አልኩት
   እሱም ይሄ ቂርአት ብዙ አስተምሮሻል ብሎ እየሳቀ እሺ ይሁና ልጄ እኔ የምፈልገዉ አግብተሽም ደስታሽን ነዉ አለኝ ቤቱ በደስታ አባቴም እናቴም እኔም ተቃቀፍን የቅድሙ ጭቅጭቅ በጠረንቤዛ ዙሪያ ዉይይት በመሰለ አጀንዳ በሰላም በፍቅር ተፈታ ቤታችን በአንዴ ወደ ቤተሰብ ፍቅር ዞረ ፡፡
    ቤተሰብም ጋር ሳያለቅሱ ሳይናደዱ ተረጋግቶ ማዉራት ጥቅም አለዉ፡፡ ግን አንዳንድ እህቶቼ ይዘሀኝ ጥፋ...እሱን ካልዳራችሁኝ እታነቃለሁ በሂወት አታገኙኝም የሚሉ አሉ፡፡ ይሄ አግባብ አይደለም ማንኛዉም ቤተሰብ ለልጆቹ ክፉ አይደለም ብቻ የትዳር ሂወት ማለት ሁለተኛ ሂወት ስለሆነ ቤተሰብም በትንሹም ቢሆን ጣልቃ መግባቱ አይቀሬ ነዉ፡፡ ትዳር ጋር አለመስማማት ቢኖር ተመልሰን የምንመጣዉ ወደ ቤተሰብ ነዉ፡፡
   
እሷ እና ጠቢቡ

#እሷ
አምላክ ልጠይቅህ ፍቅር ግን ምንድነው
ያኛውም ይሄኛውም ወደድኩሽ የሚለው
የቱ ነው የወደደኝ የቱ ነው ያፈቀረኝ
አንተው መልስልኝ እኔስ ግራ ገባኝ

#ጠቢቡ
ልጄ ተባረኪ ጥሩ ጥያቄ ነው
መውደድ በጣም ብዙ ማፍቀር ግን 1 ነው
አንቺን የሚወዱሽ ተቆጥረው አያልቁም
ያፈቀረሽ ሰው ግን ከ 1 እንኳን አይበልጥም

#እሷ
እንዲ ከሆነማ አፈቀርኩሽ ያሉኝ
ከ 1 እኮ ይበልጣሉ መጥተው የጠየቁኝ
ከነዛ ሰው ሁሉ ተድያ እንዴት ልለየው
የእውነት እፍቃሪ ምልክት ምንድነው

#ጠቢቡ
በማስመሠል ዘመን ማመኑ ቢከብድም
የእውነት ፍቅርን ግን መለየት አያቅትም
ተወኝ ብትይውም ሊተውሽ ቢፈልግ
ልቡ ግን አይፈቅድም ይሄንን ለማድረግ

አንቺን እንዲተውሽ ፊት አንኳን ብትነሺው
ፊትሽን ይተውና ልብሽን ነው የሚያየው
አፈቀርኩሽ ብሎ ፅናቱ ካልታየ
የውሸት ፍቅር ነው እለፊው ባላየ
#ምንጭ_anu

 ቅዳሜ ተሻግረን እሁድን የወፎች ጫጫታ አስተጋባ ትናንት ጀምሮ እናቴ ጋር አብሬ ደፋ ቀና እያልን ነዉ ስድስት ሰአት ላይ ስራዉን አጠቃለልን ስድስት ተኩል ሲል ከፊርዶስ ስልክ ተደወለ.... ስልኩን አነሳሁት ..ፊርዶስም ማመን የማልችለዉን በስልክ ነገረችኝ.....
ምን ተፈጥሮ ይሆን ?? የሂክማ ነገር አንዱን ፈተና ስጨርስ ሌላ የማትወጣዉ ፈተና ይመጣባታል ...

ክፍል ይቀጥላል.........


   የሂክማ ታሪክ በመጨረሻዉ ክፍል እና በማጠቃለያ ፁሁፋችን ይጠብቁን ...

https://telegram.me/mahbubil
20 views ⓵, 20:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 09:50:06 እዉነተኛ ታሪክ
  #አስለቃሽ #የቴሌግራም
              #ፕሮፋይል

      #Part



    እኔም እናቴ ጎን ቁጭ ኡልኩኝ...ሁሉንም ልነግራት ጀመርኩ ስለ ዙበይር እናቴ ዙበይር ማለት .......የፊርዶስ ታላቅ ወንድም ስለ ፀባዩ እና እስከሚሰራዉ ስራ መርካቶ ሱቅ እንዳለዉ መኖሪያ ቤትም እንዳለዉ አከራይቶት እሱ ቤተሰብ ጋር እንደሚኖር ነገርኳት፡፡
     እናቴም ጥሩ ግን ፊርዶስ በጣም ጥሩ ልጅ ናት ማሻ አላህ የነ እሱ ዘር ጋር አንቺ መጋብትሽ ደስ ይለኛል፡፡ ግን ልጄዋ አለችኝ በስስት እያየችኝ የወደድሽዉ ብር ስላለዉ ሱቅ ስላለዉ መኖሪያ ቤት ስላለዉ ነዉ ወይ ?.. አንቺ በብር አስበሽ ከሆነ አላህ ያይሻል አንቺ በብር የምትገዢ ሸቀጥ አይደለሽም እኔ የምፈልገዉ ኢማን ያለዉ አንቺን ወዶሽ በፍቅር ተሳስራችሁ ልጅ ወልዳችሁ የአንቺን ደስታ ማየት ነዉ እንጂ ገና እሱ ብር አለዉ ብለሽ አስበሽ የትዳር አጋር የመረጥሽዉ ከሆነ ልጄዋ ይቅርብሽ፡፡ እኔ ዲን ያላቸዉ አብራችሁ ማደግ የምትችሉ ሁለት ሰዉ ቅርብ ቀን ልጅሽን ዳሪኝ ያሉኝ አሉ፡፡ ልጄ እኔ የምፈልገዉ የአንቺን ደስታ እንጂ ወንድ ልጅ በብር ሀይል አግብቶሽ የሀብታም እስረኛ እንድትሆኝ አልፈልግም አለችኝ፡፡
.....እኔም እናቴን ምንም አላልኳት ወሬዋን አስጨረስኳት እዉነቷን ነዉ ትዳር ማለት ሁለተኛ ሂወት ማለት ነዉ እንጂ እንደ ሆቴል ገብቶ ተጠቅሞ የሚወጣበት ሂወት አይደለም፡፡ እናቴ ልክ ነሽ ግን ዙበይርን በብዙ ነገር ፈትኘዋለሁ እናቴ ብዙ ለአንቺ መንገሩ ጥሩ መስሎ ያልታዩኝ ሂወቶች ነበሩኝ..... ዙበይር ነዉ የተረዳኝ እሱ በብሩ የማይተማመን እኔ ለራሱ ይሄ ሁሉ እንዳለዉ የሰማሁት ቅርብ ቀን ነዉ ...የቀረበኝ ፍቅሩን ይዞ ትዳርን አስቦ እንጂ ይሄ ቤት አለኝ መርካቶ ሱቅ አለኝ ብሎ አንድ ቀን አዉርቶኝ አያቅም ማሚ በዲኑም ጎበዝ ነዉ ፡፡ የሚገርምሽ እንደ አንዳንድ ወንዶች አይደለም እናቱ ምሳ አዘጋጅተዉ ጠርተዉኝ አስተዋዉቆኛል፡፡ ለእናቱ የወደፊት ሚስቴ ናት ብሎ አሳዉቋል ማሚ እናቱም ወደዉኝ ስጦታ ሰጥተዉኛል ..ዙበይር የሚፈልገዉ እኔን ማጃጃል ሳይሆን ወደ በሀላል ወደ ትዳር ለመግባት ነዉ፡፡ እኔ ወድጀዋለሁ አንቺም ዉደጅልኝ ማሚ አልኳት፡፡
 
....እናቴም እኔ አንቺን እወድሻለሁ የወደድሽዉንም እወዳለሁ የምጠይዉንም እጠላለሁ ግን አንድ ፍሬ ልጄ ነሽ ጥሩ ትዳር እንዲኖርሽ እፈልጋለሁ ድል ባለ ሰርግ ነዉ የምድርሽ ግን ዙበይርን አምነሽበታል??? አለችኝ
...እኔም አዎ እናቴ ዙበይር ነዉ ምርጫየ ብየ ብዙ ነገሮችን አጫወትኳት ያዉ የሚደበቀዉ ያለ ሁኖ መቼም እናቴ ናት እና ሀይደር ጋር ያሳለፍኩትን እና በዛ ነገር ሀኪም ቤት የተኛሁበትን ሂወት እኔም እናቴም እንድታስታዉሰዉ አልፈልግም........

በመጨረሻም እናቴ እሺ አላህ ያሳካላችሁ አለችኝ
......እኔም ደስ አለኝ ደግሞ ደስታየን እናቴ እንዲህ ብላ ጨመረችልኝ፡፡ ዙበይር አንቺን ለእናቱ ካስተዋወቀሽ በጣም ጎበዝ አስተዋይ ልጅ ነዉ እኔንም እሁድ ምሳ አዘጋጅተን ዙበይርን አስተዋዉቂኝ እሁድ ንገሪዉና ምሳ እንጋብዘዉ   እህቱ ፊርዶስም አብረዉ ይምጡ  ...እኔም ነገ ጠዋት ደዉየ ለአባትሽ እቤት እንደመጣ እነግረዋለሁ .. አባትሽም ይወቀዉ ነገ ከሰአት መጥቶ ከአባትሽ ጋር እንመካከርበታለን  ብላ እናቴ አስደሰተችኝ

እኔም እናቴ ጋር ተቃቅፈን ሁለታችንም በጣም ደስ አለን ፡፡ እሁድ ለመድረስ ገና አራት ቀናቶች አሉ፡፡ እናቴ ለአባቴ ደወለችለት መምጣት የሚመቸዉ ቅዳሜ እንደሆነ ነገራት፡፡ ቅዳሜ አደራ እንዳቀር ለአስቸኳይ ጉዳይ ነዉ የምትፈለገዉ አለችዉ እናቴ...
.....አባቴም ለመስማት ጓጉቶ አሁን በስልክ ንገሪኝ ቢላት አይሆንም በስልክ ተነግሮ አያልቅም በአካል ስንገናኝ ነዉ የምነግርህ አለችዉ...
   ወዳዉ መኝታ ቤት በመግባት ለዙበይር ደወልኩለት ሁሉንም ነገር ነገርኩት እና እናቴ እሁድ ምሳ ትዉዉቅ እናድርግ  ብላኛለች እሁድ ይመቸሀል ከነእህትህ?? አልኩት
......እሱም በደስታ እንዴት አይመቸኝ ቤተቦችሽን ለመተዋወቅ ዝግጁ ነኝ አለኝ፡፡
.......ከዛ ለፊርዶስ ደወልኩላት ብዙ አዉርተን ...እሁድ ስላት .....ወሬየን አቋርጣ ሂኩ ታዘብኩሽ አለችኝ
ምን ሆንሽ ፊርዱ ??አልኳት
.....እሷም የምሳ ግብዣዉን መጀመሪያ ለኔ ሳትነግሪ ለወንድሜ ነግረሽ ነዋ ከእኔ እና እሱ መጀመሪያ ያወቅሽዉ እኔን አይደል ብላኝ ተሳሳቅን፡፡

የማይደርስ የለም ነገ እሁድ ነዉ ዛሬ ቅዳሜ ላይ ነን ቅዳሜ ሙሉቀን ጀምረን እኔ እና እናቴ ለእሁዱ ባሌን የማስተዋዉቅበት የምሳ ፕሮግራም ደፋ ቀና እያልን ነዉ ..አባቴንም ሸዋ ሮቢት ስለሚኖር እሁድ እቤት ምሳ ተዘጋጅቷል ምክንያቱ ስትመጣ ይነገረሀል ብለን ቅድሚያ ስለነገርነዉ ቅዳሜ ማታ እቤት ገባ፡፡

     እቤት እንደገባም ስለ ነገዉ እሁዱ የምሳ ፕሮግራም እናቴ ነገረችዉ ግን አባቴ እና እናቴ በነገዉ ምሳ ላይ የተስማሙ አልመሰለኝም ፡፡ አባቴ ጮክ ብሎ ይሄማ መቼም አይሆንም እኔ ፈቅጄ ልጄን አልሰጥም አንቺ እኔ ሳልፈቅድ ትድሪያት እንደሆነ አያላሁ...እዚህ ቤት ወንዱ ወይ አንቺ ወይ እኔ እንሆናለን አትሰቢዉ እኔን የጠየቁኝ ሰዎች አሉ እንደዉም ለአንዱ ቃል ገብቸለታለሁ ትምህርቷን ስጨርስ ብየ አሁን ከህመሟ ከሻረች እኔም አንቺን አማክርሻለሁ እያልኩ ነበር በስራ ተወጣጥሬ ነዉ እንጂ ዛሬ ላማክርሽም ነበር፡፡ ለአስቸኳይ ስትይኝ ጭራሽ ልጄ ታገባለች ብየ ትዝም አላለኝ፡፡ ወደድሽም ጠላሽም እኔ መቼም አልስማማም እኔ ለመረጥኩት ሰዉ ነዉ ልጄን የምድረዉ ...የነገዉም ምሳ ፕሮግራም እኔ አልኖርም እንደፈለጋችሁ ማረግ ትችላላችሁ...ተስማምቼ እሱን እኔ አልተዋወቅም፡፡ እናተ እሱ እቤት መጥቶ ብትተዋወቁ እኔ እና አንቺ ፍች ነዉ የሚለየን...እኔ ከሀገር ሌላ ሀገር በመንግስት ስራ የቤተሰብ ፍቅር ሳላይ በግዥ በሁቴል ምግብ የምኖረዉ አንቺ እና ልጄ እንድትደሰቱ እንዳትከፉ እንጂ ለራሴ መኖር መች አቃተኝ...ስለሆነም ይሄ የትዳር ነገር መቼም የማይሆን ነዉ ሲል እዉጭ ሁኜ ሰማሁት፡፡

የኔ ፈተና ብዙ ነዉ እኔም ከቤት ዉጭ ሁኜ ደንግጬ ቆምኩኝ...የማወራዉ ጠፋኝ ነገ ምሳ ዙበይርን ጠርቸዋለሁ....ትዳር ቤተሰብ ስቆ መርቆ ሲሰጥ ነዉ አለመግባባት ቢኖር ተመልሰን የምንመጣዉ ወደ ቤተሰብ ነዉ፡፡ ቤተሰብ ለወደደዉ ስቆ ደስተኛ ሁኖ ካልሰጠ ቡሀላ የሆነ ነገር ቢፈጠር ሌላ የቤተሰብ ጫና ይፈጠራል፡፡

....የሂክማ ፈተና በዛ አሁን ደግሞ አባቷ እኔ ያልኩት ካልሆነ አታገባም አለ..ዙበይርም ምሳ ተጠርቷል ምን ይፈጠር ይሆን በቀጣዩ ክፍል እናየዋለን

#Part

ይ...........ቀ...........
.........ጥ..........ላ................ል

Join

https://telegram.me/mahbubil
19 views ⓵, 06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-22 23:37:02 እዉነተኛ ታሪክ
  #አስለቃሽ #የቴሌግራም
              #ፕሮፋይል

      #Part



  ወደ አምስት ሰአት አካባቢ ከቤት ልብሴን ቀያይሬ ፊርዶስ ጋር አብረን ጉዟችንን ቀጠልን ..ፊርዶስም ዛሬ ምሳ እኔ ነኝ የምጋብዝሽ ብላኝ መገናኛ አካባቢ የሚገኝ  ኢስላም ሬስቶራንት(ምግብ ቤት ) ገባን፡፡ ስንገባ ግን ያየሁትን ማመን አቃተኝ አሁንም ዙበይርን ነበር ያገኘሁት፡፡ ፊርዶስም ዛሬ እስኪ ምሳ አንድ ላይ ሁነን ልጋብዛችሁ ብየ ነዉ አለችን፡፡
...... ምሳችን አዘን በላን....

ከዛም ምሳ በልተን ከምግብ ቤቱ ወጣን ፡፡ ሶስታችን ከመገናኛ ተነስተን እግራችን ወደ አመራን እየተጓዝን ነዉ...ትንሸ እንደሄድን ዙበይርም  ፊርዶስን እስኪ ሁለታችን የምናወራዉ ወሬ አለን አየር ትለቂልናለሽ አላት
...ፊርዱም ከእኔ ደብቀህ የምታወራዉ አለ ዙበይር ------እሺ ካልክ እገነጠላለሁ :: ብቻ የህዝብ ተወካዮች የፓርላማ ዉይይት እንዳታረጉት ብላ እየተሳሳቅን ገንጠል አለች
    እኔ እና ዙበይር ብቻ ቀረን ሁለታችንም ተፋፈርን በዝምታ ብዙ መንገዶች ተጓዝን ማን ወሬ ይጀምር የተባባልን ይመስል አንዳችን የወሬን መጀመሪያ መክፈቻ ዙበይር ተነፈሰ ..
....... የዛሬዉ ምሳ እንዴት ነበር ???አለኝ
.......እኔም አሪፍ ነዉ አላህ ይስጣት እህትህ ጋበዘችን አልኩት
.....እሱም ግን እኔ መኖሬን ብታቂ  ፊርዶስ ብነግርሽ ትመጪ ነበር???? ብሎ ጠየቀኝ
....እኔም እንጃ ግን እህትህ የምትለኝን እሰማለሁ ፊርዶስን የማያት እንደ እህቴ ነዉ፡፡ ስለሆነም ፊርዶስን ያለችን እንቢ የምልበት ድፍረት የለኝም አልኩት፡፡
.......ማሻ አላህ እህቴን እኔም አንቺም እንወዳታለን ፊርዶስ በቤተሰብ የመጣ ትዳር አለ ግን ሁሌ የምትለዉ እኔ ከማግባቴ በፊት ወንድሜን ዙበይርን ደግሼ ድሬዉ ነዉ የማገባዉ ትላለች ፡፡ የእኔ እና እሷ አስተዳደግ የተለየ ነዉ ተከታታይ ስለሆን ተዋደን ነዉ ያደግነዉ ..አሁንም ድረስ ወንድሞቼን ሁሉንም በአንድ አይን ብታይም እሷ ግን እኔ ጋር አስተዳደጋችን የተለየ ስለሆነ በጣም ነዉ የምንዋደደዉ ሚስጥር አደብቀኝም እኔም አልደብቃትም አለኝ፡፡
......እኔም ፊርዶስን እንደ እህቴ ነዉ የማያት የምደብቃት የለኝም አልኩት፡፡
አሁን መፈራራት የለም ሁላችንም ግልፅ ሁነን እያወራን ነዉ፡፡
......ዙበይርም ግን ይሄን  ጥሩ ፀባይ  ይዘሽ እስከአሁን እንዴት ነዉ እንደ እኔ በፍቅር የወደቀ አላስቸገረሽም??? እንዴ አለኝ እየቀለደ ....
      እኔም ለዙበይር ምንም ላልደደብቀዉ ወስኛለሁ፡፡ እኔም የፈነዳ የመኪና ጎማ ይመስል ኡፍፍፍ ብየ #የት_ይደርሳል_የተባለዉን_ዛፍ_ቀበሌ_ቆረጠዉ፡፡ አልኩት፡፡
.....ዙበይርም ማለት አልገባኝም??? አለኝ
.....እስከ አሁን የት እደርስ ነበር ግን በመሀል ዛፍም ያድጋል ብለሀዉ ሲቆረጥ ማደጉ ያቆማል ይደርቃል  የኔም ሂወት እንደዛ በለዉ አልኩት
..ዙበይርም እንዴ እንደ እሱ አይደለም ዛፍ ሲቆረጥ ሌላ ያወጣል ያቆጠቁጣል አለኝ
...እኔም የኔ አቆራረጥ እንዳያቆጠቁጥ ነዉ ብቻ በሂደት ያንን ማስረሻ እህትህን ሰጠኝ አልሀምዱሊላህ አልኩት
...እሱም በአላህ ተወኩል ነዉ አላህ ያለዉ ነዉ የሚሆነዉ ደግሞ ያሰብሽበት ግብ ለመድረስ የትናንት ትናንት ነዉ አሁን ያለሽዉ አሁን ላይ ነዉ ያለፈ ትዝታ ትርፉ ቁጭት ነዉ፡፡ የወደፊት ራዐይ ግን ተስፋ ነዉ አለኝ፡፡
.....እኔም ኢንሻ አላህ ግን እስከ አሁን አንተ ለምን አላገባህም ???? ማስተዳደሪያ ብርም አለህ ነጋዴ ነህ መኖሪ ቤትም አለህ አከራይተህ ነዉ የምትኖረዉ ለምን እስከ አሁን አላገባህም??? አልኩት
    እሱም እኔ የምመኘዉ ዱአየ አላህ የምወዳትን ልጅ መጀመሪያ የወደድኳትን የትዳር አጋሬ አርግልኝ ነበር የምለዉ .....ግን ብዙ አመታት ማንም ሴት ልቤ ዉስጥ ገብቶ አያቅም ነበር....ግን ከትንሽ ወራት በፊት አንዲት ልጅ ወደድኩኝ ግን ምን ዋጋ አለዉ ፍቅሩ እኔ ጋር ብቻ ሆነ ፡፡ የአንድ ሰዉ መዉደድ ማለት በአንድ እጅ እንደማጨብጨብ ነዉ ዱአ አርጊልኝ ልጅቱ እንደምወዳት እንድትረዳኝ አለኝ፡፡
......እኔም እንደዚህ ሲለኝ እንዴ እኔን ነዉ ወይስ ሌላ ናት ብየ ተወዛገብኩ ለምን እንደሚወደኝ አቃለሁ ደግሞ እኔ ጋር ሁኖ ስለ ሌላ ሴት ያወራኝ መሰለኝ
....እኔም እስከ አሁን ስትወድ የመጀመሪያህ የሆነችዉን ለማግባት ወስነሀል ማለት ነዉ?? አልኩት

እሱም አዎ ወስኛለሁ ልጅቱን እኮ ታቂያታለሽ አለኝ፡፡
...እኔም ማን ናት??? አልኩኝ ፈጠን ብየ
........እሱም ገምች አለኝ
......እኔም መገመት አልችልም አንተዉ ንገረኝ አልኩት
....እሱም ሂኩ አንቺ ነሽ ለምን አትረጂኝም አንቺ በፍልጥ ካልሆነ በፈሊጥ አይገባሽም ማለት ነዉ?? አለኝ ፈገግ እያለ.....
     ግን አንተ እኔን የወደድክብኝ ምክንያት መስፈርቱ ምንድን ነዉ ዙበይር እንዴት የትዳር አጋርህ እንድሆን መረከኝ???? አልኩት...
......እሱም ሂኩ እኔ ከሆነሉም የወደድኩሽ ግልፅነትሽ እና ዲን ስላለሽ የዛሬወን ሳይሆን የነገዉን ሂወት የምታስቢ ነሽ ፡፡ ፊርዶስ በጣም ትወድሻለች ታከብርሻለች ፊርዶስ የወደደችዉ ለኔ የወደፊት ትዳሬ ከሆነ ደስተኛ ነኝ ፡፡ ፍቅር መቼ ?የት ?እንዴት ?ከየት? ወደ የት? የማይባል ግዑዝ ነገር ነዉ አላህ ፍቅሬን በሀላሉ አድርጎ የትዳር አጋሬ ብትሆኝ እድለኛ ነኝ ሂኩ አለኝ
......እኔም የደስታም የሀዘንም እንባ ከየት መጣ ሳይባል በአይኔ እንደምንጭ ዉሀ ኩልል እያለ ወረደ .... ሳለቅስ ዙበይር ደነገጠ ምን ሆንሽ ??መናገር የለብኝም ነበር እንዴ?? ምን ላርግ ተቸግሬ ነዉ ሂኩ አለኝ፡፡
ያለቀስኩት በእሱ መወደዴ የደስታ እምባ ሲሆን በተዘዋዋሪም እኔ ደግሞ ለትዳር ብቁ አይደለሁም ዙበይርን እኔም እወደዋለሁ ግን የኔ እንደማይሆን በማሰብ በዉሸት መዉደድ ጉድ የሰራኝ ሀይደር እዉነተኛ እኔን የሚወድ ሳገኝ  የተደበላለቀ ሁለት ስሜት ያለዉ እምባ ነዉ፡፡
    ግን ዙበይርን ልዋሸዉ አልፈለኩም፡፡ ልነግረዉ ወሰንኩ እሱም አረ በፈጠረሽ አታልቅሺ አታስጨንቂኝ ይለኛል ዙበይር፡፡
.....እኔም እምባየን በክሪሜ አበስ አድርጌ >>>>>> ዙበይር እኔ ለአንተ አልሆንህም ሌላ ፈልግ እኔ አንተን ባገባህ ደስ ይለኝ ነበር ግን ....ብየ ልቀጥል ስል
.......ሂክማ አሁን ያለነዉ ዛሬ ጋር ነዉ ሁሉንም ፊርዱ አስረድታኛለች ......እምባሺን ጥረጊ ብሎ ለመጀመሪያ ጊዜ በእጁ እምባየን ጠረገልኝ......አይን አይኔን እያየ ሂኩ ብቻ ዉደጅኝ አንቺን ማጣት አልፈልግም
ዛሬ ቁርጤን ንገሪኝ ሂክማ እኔ እወድሻለሁ..እኔ እስከማንነትሽ ተቀብየ አንቺ ጋር ጥሩ የፍቅርሽ ተካፋይ የትዳር አጋሪ ልትሆኝ ዝግጁ ነሽ ???...የአንቺን ልብሽ ዉስጥ ያለዉን ስለ እኔ ያለሽን ስሜት ንገሪኝ ...ዛሬ ዉሳኔሽን አሳዉቂኝ አለኝ....

ሂክማ የመጨረሻ ዉሳኔ ትሰጣለች ምን ትወስን ይሆን ?? በሚቀጥለዉ ክፍል እናያለን

#part

#ይ.............#ቀ...............
.........#ጥ.............#ላ...................#ል

https://telegram.me/mahbubil
21 views ⓵, 20:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 22:54:17 እዉነተኛ ታሪክ
  #አስለቃሽ #የቴሌግራም
              #ፕሮፋይል

      #Part



     ከፊርዶስ ጓደኛ ከሂክማ የበለጠ ቆንጆ አዲስ አበባ ብፈልግ አታገኝም ብለዉ ሁሉም ሲስቁ ነገሮች ሁሉ እኔን እንደሆነ ጠረጠርኩ፡፡

ከዛም ምሳ በልተን ጨረስን ግን ሌሎቹን ሁለቱን የፊርዶስ ወንድሞች እቤት የሉም፡፡ ይሄ program ለኔ እና ለዙበይር በዛዉም እናቲቱ እኔን እንዲያቁኝ የተዘጋጀ ዝግጅት መሰለኝ፡፡
   እስከ አሱር ድረስ እነሱ ቤት ፊርዶስ እና እናቷ ጋር እየተጨዋወትን ቆየን፡፡ አሱር እነሱ ቤት ሰግደን ወደ ቤት ልሂድ ተነሳሁ.... ላደረጉልኝ የምሳ ግብዣ አላህ ይስጥልኝ ብየ ከቤት ልወጣ ስል ..... የዙበይር እና ወይዘሮ ዚነት ልጄ እስኪ አንድ ጊዜ ከመኝታ ክፍል እቃ ይዤ ልምጣ ጠብቂኝ ብለዉ ወደ መኝታ ክፍል ገቡ
እኔም እሺ አልኩኝ
.....ማዘር መጡ የሚያምር አበያ ሰጡኝ ልጄ ልበሽዉ የልጄ ፊርዶስ ጓደኛ አይደለሽ በትንሹም ቢሆን ማስታወሻ ይሁን ይሄን አበያ  ባየሽ ቁጥር እኔን እያስታወሽ ዱአ እንድታረጊኝ እና መጥተሽ እንድዘይሪኝ እፈልጋለሁ እኔ ከአንቺ ዝምድናዉን እፈልጋለሁ ብለዉ ግንባሬን ሳሙኝ፡፡
እኔም ማዘር አመሰግናለሁ ብየ ተቃቅፈን ተለያየን ፡፡ ፊርዶስ እና ዙበይር እኔን ሊሸኙኝ አብረዉ ከእነሱ ቤት ወጥተን ጉዟችንን ጀመርን ..

እያወራን እየተጠዋወትን እየሄድን ፊርዶስ አንድ የምታቃት ልጅ አግኝታ አሰላሙ አለይኩም ተባብለዉ ተዘያየሩ እዛዉ ቁመዉ ማዉራት ጀመሩ፡፡
 ፊርዱ እደርስባችሇለሁ እየሄዴችሁ ጠብቁኝ ከምቆሙ አለችን ፡፡ እኔና ዙበይር ብቻ ሁነን ወደ ፊት ጉዟችንን ቀጠልን ከአሁን አሁን ፊርዱ ትመጣለች ብየ ብዞር እዛዉ ቁማለች እርምጃ በተራመድን ቁጥር ፊርዶስን እየራቅናት መጣን እኔ እና ዙበይር ብቻችንን ሆንን ፡፡ ዙበይርን ወድጀዋለሁ ግን የበፊት ማንነቴ ያስፈራኛል ....እሱም እንደሚወደኝ አዉቃለሁ ግን ዉዴታ ሙሉ የሚሆነዉ አብሮ በትዳር መዝለቅ ሲቻል ነዉ፡፡ ብቻ እኔም ቀጥ ስል አይን ለአይን እንጋጫለን ሁለታችንም አንገታችንን እንደፋለን፡፡

ዙበይር የዝምታዉን ድልድይ ለመስበር እየታገለ ነዉ........ሂክማ ተጨዋቺ ወሬ አምጪ ፊርዶስ እንደሆነች ወሬዋን ከጓደኛዋ ጋር እያወራች ነዉ፡፡ በጣም ከእሷ ርቀት አለን የምመጣ አይመስልም  አለኝ፡፡
......እኔም እሺ እጫወታለሁ እልኩት
.........ምሳ እንዴት ነበር??? አለኝ
.............አሪፍ ነበር ጀዛከሏህ አለኩት
አንድ አንድ እያልን በወሬ ተግባባን፡፡ ግን በመጨረሻ ከበድ ያለ ጥያቄ ጠየቀኝ፡፡ ሂክማ ግን ሰለፍቅር ምን ታስቢያለሸ ????አለኝ .....
....ይህን ንግግሩን ስሰማ በጣም ደነገጥኩ የምመልሰዉ ግራ ገባኝ፡፡ ዝም አልኩኝ
.......ሂክማ ምነዉ የማይጠየቅ ጥያቄ ጠየኩሽ እንዴ??? አለኝ
...... አኔም ካላስቸገርኩህ የጠየከኝ መጀመሪያ አንተ ነህ ግን ይህን ጥያቄ አንተ መልስልኝ ስለፍቅር ምን ታስባለህ ???መልስልኝ እና እኔም መልስ እሰጥለሁ አልኩት፡፡
----------------እሱም ፍቅር ሳፈልጊዉ ጊዜ ሰአት ቦታ ሳይል የሚይዝ ነዉ:: ግን ችግሩ ያፈቀረዉ ሰዉ እንዴት እንደሚወድ ለተፈቃሪዉ ግልፅ አለመሆኑ ነዉ; እኔ የወደድኩትን ያፈቀርኩትን የመጀመሪያየ የሆነችዉን ልጅ   እስከ ሂወት አጋሬ የልጆቼ እናት ብትሆን ደስ ይለኛል ....አንቺሰ ምን ታስቢያለሽ???? አለኝ
  ሀይደር ጋር ያሳለፍኩት ያጠባሳ ጊዜ ትዝ አለኝ፡፡
........ከዛም ዙበይር እኔ ለፍቅር ወንድን የምቀበልበት ልቤ ዉስጥ የማስቀምጥበት ቦታ በጣም ተጎድቷል አልኩት፡፡ አንተንም የቀረብኩህ የፊርዶስ ወንድም ስለሆንክ ነዉ፡፡ አንተ ለኔ የጓደኛየ ወንድም ነህ ከዚህ ዉጭ እኔ ብዙ ያለፉ ሂወቶች የተበላሹ ማንነቶች አሉኝ እኔ ለእንደ አንተ አይነት ጥሩ ወንዶች አልገባም አልኩት፡፡ ምንም አማራጭ የለኝም እየፈለኩት የማጣት አይነት ስሜት ይሰማኛል፡፡
........ዙበይርም እኔ እስከዛሬ ደበኩት ግን መደበቄ ለኔ እንቅልፍ ነሳኝ ዛሬ ለአንቺ ልነግርሽ ዝግጁ ነኝ ሂክማ ይህን ስነግርሽ ከኔ ላትርቂ ላትሸሺ ቃል ግቢልኝ፡፡ ሂክማ እወድሻለሁ አንቺን አጥቼ መኖር አልፈልግም እባክሽ ተረጂኝ እና ቀጥታ ወደ ትዳር እንግባ አግብቼሽ የወደፊት ሚስቴ እንድትሆኝ እፈልጋለሁ ከአንቺ  ልጆች መዉለድ እፈልጋለሁ፡፡የዛሬዉ ምሳ እናቴ የወደፊት እጮኛህን አስተዋዉቀኝ እያለች ስረብሸኝ አንቺን ስለመረጥኩ ነዉ ምሳዉ እናቴ ለማስተዋወቅ የተዘጋጀ ነዉ ......አለኝ አንገቱን ደፍቶ

እኔም ዝም ብየ አንገቴን ደፍቼ የሚለኝን እየሰማሁ ነዉ ዙበይር በእድሜም እኔን ቢበልጠኝ ሶስት አመት ነዉ ከዚህ በላይ አይበልጠኝም በጣም አይናፋር ሲሆን ስራዉም መርካቶ ላይ ደርዘን ልብስ ማከፋፈል ነበር፡፡ ግን እኔ ዙበይርን ማግባት አልችልም ለምን ቢጠይቀኝ መልስ የለኝም፡፡ እኔም አንገቴን እንደ ደፋሁ እንባየ ይወርድ ጀመር
....ዙበይርም ደነገጠ
እንዴ በነገርኩሽ ነገር አስከፋሁሽ እንዴ ???እኔም ተቸግሬ ነዉ ሂክማ እንድታለቅሺ ሳይሆን እንድትረጂኝ ነዉ ፡፡
--------------እኔም ዙበይር ሌላ ፈልግ እኔ ለትዳር አልሆንህም .....እኔ እና አንተ አንድ ላይ መኖር አንችልም ብየ ከእሱ በተቻለኝ አቅም እየሮጥኩ ሄድኩኝ

.....ዙበይርም ሂክማ እያለ ሲከተለኝ፡፡ ዘወር ብየ እንዳትከተለኝ ብየ ተቆጣሁት..ዙበይርም ባለበት እንባዉ እየወረደ ቁሞ ቀረ.....

#እንዲህ #አድርጎኛል
ተፃፈ  በ ዘ አዶኒ

ፍቅርሽ እያቃዠ እንቅልፍ ያሳጣኛል
ከእህል ከውሃ ጋር ዘወትር ያጣላኛል
ሆዴን ባርባር እያለ ደርሶ ይጨንቀኛል
በዓለም ለብቻዬ የተተውኩ ይመስለኛል

በውድቅት ሰዓት ከቤት እወጣለው
ፍቅርሽን ፍለጋ ሌሊቱን እሄዳለው
ተጉዤ ሲደክመኝ ኮከብ እቆጥራለው
ለጨረቃ ሳልፈራ የሆዴን እነግራታለው
ጉልበቴን አዝሎ አቅም ነስቶኛል
ቅስሜን ሰባብሮ ወኔ አሳጥቶኛል
የፍቅር ቅጣት ህመሙ መሪር ነው
መጨረሻው ካማረ ሁሉም ለበጎ ነው

ግና እፈራለው ብኩን ሆኜ እንዳልቀር
አይሰምርም ይባላል የአንድ ወገን ፍቅር
ብቻ አለው ዛሬም እኔ እንዳለሁኝ
ህመሜን አይቶ ማንም ሳይጠይቀኝ
የሆንኩትን ሁሉ መግለፅ ቸግሮኛል
ፍቅርሽ በጥቂቱ እንዲህ አድርጎኛል፡፡

#part

https://telegram.me/mahbubil
ይ.............ቀ...............
.........ጥ...............ላ.......................ል
17 views ⓵, 19:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-13 09:29:42 እዉነተኛ ታሪክ
  #አስለቃሽ #የቴሌግራም
              #ፕሮፋይል

      #Part




      ስልኩን አነሳሁት የወንድ ድምፅ ነዉ፡፡ ድምፁም የማቀዉ ድምፅ ነዉ፡፡ ስልኩን እንደያዝኩት ደንግጬ  ቆምኩ...የደወለልኝ. ዙበይር ነዉ
አሰላሙ አለይኩም
....እኔም ወአለይኩም ሰላም አልኩት
...እንዴትነሽ.... እንዴትነህ ከተባባልን ቡሀላ በሰላም ነዉ መደወሉ?? አልኩት
...መደወል አይቻልም እንዴ ??ስልክሽን ከእህቴ ፊርዶስ ነዉ የተቀበልኩት አለኝ.... አንዳንድ ወሬ አዉርተን ብዙም በስልክ በወሬ ሳንቆይ ቻዉ ተባብለን ስልኩን ዘጋሁት፡፡
ዙበይር በኔ ፍቅር ወድቋል ከንግግሩ ያስታዉቃል በጣም ደንግጧል፡፡
ዙበይር በሂክማ ፍቅር ወድቋል ግን እስከ ማንነቷ ይቀበላት ይሆን ????
#ናፍቆት .
ናፍቀሽኛል ብዬ ቃላት እያወጣሁ
ናፍቆቴን ለመግለፅ ለናፍቆት ቃል አጣሁ
ገና ናፍቀሽኛል ብዬ ሳልጀምረው
ተሰማኝ ናፍቆትሽ ውስጤን ሲያሸብረው
እኔ የፍሬ ናፍቆት ፣ አንቺ የጥበብ ሸማ
ሲመታ አዳምጪው ያን የልቤ ዜማ
በናፍቆት አለንጋ
ደምቶ የማይረጋ
ብዙ ቅኔ ያለው ናፍቆት ሞልቶት ልቤን
ናፈቅሽኝ እላለሁ ላይገልፀው የውስጤን
የመናፈቄን ጥግ የጉጉቴን መጠን
የመውደዴን አቅም የናፍቆት ወሰን
ድንበሩን ለማየት መግለጥ ያሻው ዶሴ
ከምን ደርሶ እንደሆን ይለካ እስትንፋሴ ።

      ዙበይር እንዴት ሊደዉልልኝ ቻለ???? ለፊርዶስ ሂወቴን ከላይ እስከታች ነግሪያት እንዴት ስልኬን ሰጠችዉ ????እያልኩ ተወዘገብኩ፡፡ የማይነጋ የለም ነጋ ፊርዶስ ጋር ተገናኘን ከዛ ስለማታዉ ጉዳይ ዙበይር ደዉሎልኛል ብየ ከነገርኳት ቡሀላ .... እንዴት ለወንድምሽ የኔ ቁጥር ትሰጫለሽ??? ሂወቴን አጫዉቸሽ ነግሬሽ ወንድምሽ እኔን እንዲረሳ ማረግ ሲገባሽ ..ይባስ ብለሽ ስልክ ቁጥሬን ሰጠሽዉ ፊርዱ ጥሩ መስሎ አይታየኝም አልኳት፡፡
  ....ፊርዱም በመቆጣት ከአሁን ቡሀላ ስለ አለፈዉ ሂወትሽ ነግረሽኛል ተረድቸሻለሁ ጨዋና እና ሬድዮ ወሬ አይደጋግምም አይደል የሚባለዉ ..ወደ አላህ ተመልሰሻል ያለፈዉ አልፏል አሁን ያለነዉ ዛሬ ላይ ነን፡፡ አንድ ሰዉ ትናንት ያየዉን ህልም ዛሬ ላይ መድገም አይችልም ፡፡ ሂኩ ከአሁን ቡሀላ ያለፈ ሂወት ብታነሽብኝ የምወድሽን ያህል እጠላሻለሁ፡፡ አንቺ ለኔም ለወንድሜም ለማንም ሰዉ ወንጀለኛ መጥፎ ሰዉ አይደለሽም እንደዉም ጠንካራ ጎበዝ ነሽ ፡፡ ሲደዉልልሽ ፊት አትንሽዉ ዙበይር ወንድሜ አንቺም እንደ እህቴም እንደ ጓደኛየም የማይሽ ነሽ ሁለታችሁም እንድትጎዱ አልፈልግም አለችኝ፡፡
.....እኔም እሺ ከአሁን ቡሀላ ያለፈ ሂወቴን ላነሳ ብየ ፊርዱ አንገት ስር ጥምጥም ብየ አለቀስኩኝ፡፡

ዙበይር ጋር በስልክ ሲደዉልልኝ ማዉራት ጀመረን ዙበይር እንደሚወደኝ አቃለሁ እኔም ትንሽ ለዙበይር ከሌሎቹ ወንዶች ለየት ያለ አመለካከት አለኝ፡፡ ግን ያንን ጥያቄ ቢጠይቀኝ ምን እንደምመልስ አላቅም.... ግን ፊረዱ ያለፈዉ አልፏል አሁን ወደፊት እሰቢ ብላ አስጠንቅቃኛለች፡፡ ዙበይር እንደሀይደር ወደድኩሽ አበድኩልሽ ሳይሆን የጨዋ ወንድ አነጋገር ነበር የምናወራዉ፡፡እያደር ግን ስልክ አዉርተን ስንጨርስ ሂኩ እንደምወድሸ እንዳረሺ ማለት ጀምሯል፡፡ እኔም አረሳም ብየ እጥር ያለ መልስ እመልስለታለሁ፡፡
,
አንድ ቀን ፊርዶስ እሁድ ምሳ እኛ ቤት ጋብዠሻለሁ አንቺ እናትሽን አስተዋወቀሽኛል እናትሽ እኔን የምታየኝ እንደ ልጇ ነዉ ፡፡ እኔ እኮ አላስተዋወኩሽም አለችኝ፡፡
እናም እሁድ ምሳ ጋብዠሻለሁ ቤታችንን ስለማታቂዉ አብረን እንሄዳለን አለችኝ
፡፡ እኔም እሺ ከማለት ዉጭ ምንም አላልኩም፡፡
  

እሁድ ደረሰ ፊርዶስ እኛ ቤት መጥታ አብረን ወደ እነሱ ቤት ወደ  ጎሮ ሰፈር ሔድን ፡፡ ቤታቸዉ ደረስን ቤታቸዉ በጣም ያምራል አባቷ ነጋዴ ነዉ፡፡ ከዟም እናቷ ወይዘሮ ዚነትን አስተዋወቀችኝ ተነስተዉ ጉንጬን ሳሙኝ
... ሂክማ እኔ ልጄን ፊርዶስን በአሳታዋይነቷ በጣም እወደታለሁ ደግሞ ፊርዶስ አንቺን ትወድሻለች ልጄ የወደደችዉን እኔም እወዳለሁ በአካል ዛሬ ስላወኩሽ ደስ ብሎኛል ፡፡ ደግሞም ቆንጅየ ነሽ ማሻ አላህ ብያለሁ አሉኝ ወይዘሮ ዚነት፡፡ እኔም አመሰግናለሁ ማዘር ብየ ግንባሬን ሳሙኝ፡፡ ምሳዉ በጣም ለየት ያለ ዝግጅት ነበር ምሳዉ ቀረበ

--------- ከዉጭ አሰላሙ አይኩም የሚል ድምፅ ሰማሁ ከዛም ወደ ቤት ገባ ፡፡ ወአለይኩም ሰላም ምሳ ላይ ደርሰሀል ና ምሳ ብላ አሉት እናቱ
......እሱም እሺ ብሎ ታጥቦ እኛ ጋር ቀረበ ...እናቱም መቼ ይሆን አንተ ጎጆ መስርተህ ምሳ የምጠራን ዙበይር አሉት
.....ዙበይርም እማየ ዱአ አድርጊ መስመር ላይ ነኝ አላህ ያሳካልህ ብለሽ አላት እናቱን....
ፊርዶስም ከአፉ ቀበል አድርጋ እንዴ ትገርማለህ እኔ የማላቃት ያላስተዋወከኝ ከእህትህ ደብቀህ ያመጠሀት ሚስትማ እኔ አልስማማም አለች ፊርዱ
....ዙበይርም ከአንቺማ ምንም አይደበቅ ፊርዱ እኔ እኮ ታናሽ እህቴም ብትሆኝ አከብርሻለሁ አንቺ የወደድሽዉን ነዉ የምወደዉ አላት ለፊርዶስ፡፡

ወሬዉ እናታቸዉ ዙበይር ፊርዶስ እየተቀባበሉ ስለትዳር ነዉ የሚያወሩት እኔም የሚሉትን ሳዳምጥ ነገሮች ሁሉ ወደ እኔ ያመላከቱ መሰለኝ፡፡ እናቲቱ ማብቂያ ላይ ያሉት ንግግር ገረሞኛል መቼም ከፊርዶስ ጓደኛ ከሂክማ የበለጠ ቆንጆ በሸገር ብትፈልግ አታገኝም ብለዉ ሁሉም ሲስቁ ነገሮች ሁሉ እኔን እንደሆነ ጠረጠርኩ፡፡ዙበይር እና ፊርዶስ  እኔ እና ዙበይር ለወደፊት አብረን ለመኖር መስመር እንደጀመርን እናታቸዉ ቅድምያ ነግረዋቸዋል ማለት ነዉ ?? ይሄ ነገር ባይሳካስ?? ለእናታቸዉ ተናግረዉ ይሆን እንዴ ???እያልኩ እዛዉ እነሱ መሀል ቁጭ ብየ በሀሳብ አለም ዉስጥ ተጓዝኩኝ....

#part

ይ.............ቀ...............
.........ጥ...............ላ.......................ል

https://telegram.me/mahbubil
21 views ⓵, 06:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 23:43:11 አሰላሙ ዐለይኩም ጀመዓ

''2ኛ ዙር
በአሏህ ፍቃድ በቅርብ ቀን 2ኛ ዙር የውድድር ፕሮግራማችን ይጀምራል
የውድድሩን ሁኔታ ህግ እና አፈፃፀም
እናሳውቃለን እንዲሁም የሽልማት እድገትም አድርገናል እናሳውቃለን እስከዛው ቻናላችንን ጆይን መልዕክታችንን ሼር እያደረጋቹህ ቆዩን።

@mahbubil
15 views ⓵, 20:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 01:08:18 እዉነተኛ ታሪክ
  #አስለቃሽ #የቴሌግራም
              #ፕሮፋይል

      #Part


እኔ ከተቀመኩበት ስነሳ ፊርዶስ አብራኝ ተነስታ .......
እንባየን ከጉንጬ እየጠረገች ሂኩየ አንቺኮ አሁንም ንፁህ ሰዉ ነሽ ወንጀል ሸይጧን አሳስቶሽ ልሰሪ ትችያለሽ ግን ወደአላህ ተመልሰሽ ማረኝ እያልሽ እያለቀሽ ነዉ፡፡ አላህ መሀሪ ነዉ የወንጀል ጉዳቱ ወንጀል መሆኑን እያወቁ እዛዉ ያለተዉበት በዛዉ ወንጀል ላይ ሁኖ ሳይቶብት መቼ እንደምንሞት ሳናቅ ዛሬ ወይ ነገ እቶብታለሁ እያልን ወይም ሀዲስ ስንሰማ መስጊድ ስንገባ ደአዋ ስናዳምጥ አልቅሰን ወንጀሎኞች ነን ከአሁን ቡሀላ ወደ ወንጀል አልሄድም ብለን እንቶብታለን ግን ወይ ከመስጊድ ስንወጣ ወይ ደአዋዉ ሲያልቅ የቶበትነዉን እንረሳዉና ወደ እዛ ወንጀል እንሄዳለን ይሄ አይነት ደግሞ መቶበት ሳይሆን በራስ ጭንቅላት ላይ ጌም እንደመጨዋት ነዉ...አሁን ብዙ ሰዉ ጋር የሚታየዉ ጥርት ያለ ተዉበት ሳያረጉ  መሞታቸው ነዉ፡፡
........ሂኩየ አንቺ ከእነዚህ ሰዎች ትለያለሽ ወንጀል ሰርተሽ  ወደ አላህ ነዉ እያለቀሽ ያለሽዉ እንጂ ወንጀል አብራችሁ ወደ ሰራሽዉ ሰዉ አይደለም ስንት እህቶቻችን ይህን ወንጀል ሰርተዉ ወንጀል ከሰሩት ሰዉ ጋር ተጣብቀዉ አንተዉ ቅብረኝ እሞታለሁ መርዝ እጠጣለሁ የሚሉ የፈጠራቸዉን ጌታ የረሱ አሉ አይደል፡፡ አንቺ እኮ የምታለቅሽዉ ወደ ፈጠረሽ ጌታ ወደ አላህ እንጂ ወደ ሀይደር አይደለም ስለሆነም አንቺ ከሌሎቹ ሴቶች ልዩ ነሽ፡፡
ከቦታና ከ አቅጣጫ ጥራት የተገባዉ አላህ ጌታችን እንዲህ ይላል፦ የባሮችን ጉዳይ ተውልኝ እስኪ ከነሱ ወደኔ የተመለሰ (የተፀፀተ) እኔ ወዳጁ ነኝ። እኔኮ እናት ለልጇ ከምታዝነው በላይ ለባሮቼ አዛኝ ነኝ። ብሏል። ሂኩየ ፡፡ ስለሆነም ከአሁን ቡሀላ የአንቺን ለቅሶ ሳይሆን የምፈልገዉ ደስታሽን ነዉ ሂኩየ አንቺ ከአሁን ቡሀላ የረከሽ ወንጀለኛ አይደለሽም ልታለቅሺ ሳይሆን.... የባሰ አለ ብለሽ ልታመሰግኚ ነዉ የሚገባዉ  አንቺ ልታለቅሺ አይገባም አላህ መሀሪ አዛኝ የሆነ ጌታ ነዉ ብላ አንገቴ ስር ጥምጥም አለችብኝ፡፡ ከዛም ወደ ቤቴ ልሂድ ብላኝ ሸኝቻት ተመለስኩኝ፡፡

   ዉይ ለፊርዶስ ከነገርኳት ቡሀላ ይህ ሚስጥር ተሸክሜዉ እንእንዳታሳርየተባልኩፊመስል አፍኘዉ ኑሮ ቅልል አለኝ ፡፡ ዲፕሬሽን ዉስጥ ነበርኩ አንድ ሰዉ ዲፕሬሽን ዉስጥ ከሆነ መፍትሄ ይሰጠኛል ብሎ የሚያማክረዉ ሰዉ ከነገረዉ 50% ከዲፕሬሽን ይላቀቃል፡፡ የሆነ የደስታ ስሜት ተሰማኝ

ማታ ላይ ልተኛ ስል ፊርዶስ ደዉላልኝ በቃ በደስታ አወረሇት ..
.....እሷም ሂኩ ምን ተገኘ ደስተኛ ሁነሻል ??? ስትለኝ
......ምንም አልተገኘ ግን ቅልል ብሎኛል የደስታ ስሜት ተሰማኝ አልኳት ፡፡ ብዙ ነገሮችን አወራን ስንጨርስ በስልክ ተሰነባብተን ወደ መኝታየ አመራሁ
ለመጀመሪያ ጊዜ ሳልጨናነቅ ደስተኛ ሁኜ አደርኩ፡፡ የመጀመሪያ የደስታ ሂወት የጀመርኩ ይመስለኛል አልሀምዱሊላህ ተገላገልኩ..... ዙበይር ከአሁን ቡሀላ ተስፋ ይቆርጣል ፊርዶስ እዉነቱን ትነግረዋለች ወደ እኔ በጭራሽ አይደርስም ብየ እራሴን አሳመንኩት፡፡
    ሳስበዉ የቸገረን የልባችንን የምነነግረዉ ለአላህ ብለን የምንወደዉ በአላህ መንገድ በዲነል ኢስላም ያገኘነዉ ጓደኛ ነዉ፡፡ ማንኛዉም ሰዉ አንድ የልብ ጓደኛ ያስፈልገዋል በደስታዉም በሀዘኑም ከጎኑ የሚሆን ሀሳብ ሲያስብ የማያማክረዉ በሀሳቡ ገንቢ አስተያየት መስጠት የሚችለዉ  ሰዉ ለሌላ ሰዉ መድሀኒት ነዉ ፡፡ ተማክረዉ የፈሱት ፈስ አይሸትም አይደል የሚባለዉ የልብ ጓደኛ ወሳኝ ነዉ፡፡ ጓደኛ ማለት በክፉም በደስታም በሀዘንም አብሮ መግባባት ሲቻል ነዉ፡፡ መጠንቀቅ ያለብን ሴቶች ማንኛዉም ነገር እስከ ዚና መስራት ወንጀል ድረስ የሴት ጓደኛ ተፅእኖ ግፊት ነዉ ጥሩ ሴቶች እየተበላሹ ያሉት በመጥፎ ሴቶች ጓደኛ ይዘዉ ነዉ፡፡ 
       የአሁን ጓደኝነት ስታማክረዉ ወይ ሚስጥርህን ለሌላ ያሳልፈዋል ወይም በቀኝ ጆሮዉ አዳምጦ በግራ ጆሮዉ ያፈሰዋል፡፡ .የቱርክ ልብስ ማን ልበሺ አለሽ?? ጓደኛየ....የያሽዉ የወንድ ጓደኛ ማን አስተዋወቀሽ?? ጓደኛየ...ሶላት አልሰገድሽም የት ነበርሽ?? ጓደኛየ ቤት....ሜካፕ ሊፒስቲክ ኮስሞቲክስ ማን እንድትቀቢ አስለመደሽ ???ጓደኛየ.......ዚና እንድሰሪ ማን አስተዋወቀሽ ???ጓደኛየ...ነዉ መልሳችን፡፡ አሁን የያሽዉ የሴት ጓደኞችሽ ከስንት አንድ ካልሆነ ከነዚህ ዉጭ ያሉት ብዙዎቹ ሴቶች የሚሸወዱት የሚበላሹት በሚይዙት የሴት ጓደኛ ስበብ እንደሆነ መገንዘብ አለብን፡፡
     ሴትን ለሴት እሾህን ለሾህ አይደል የሚባለዉ በጓደኛ አመራረጥ ቢያንስ እንደፊርዶስ አይነት ጓደኛ መያዝ መቻል አለብን፡፡
አሁን ላይ ትዉልዱ ከቤተሰብ ቁጥጥር ዉጭ ሁነናል ጊዜዉ የተራቀቀ ነዉ በፊት ቤተሰብ ይቆጣጠረን ነበር አሁን ግን በስልክ ሁኗል ስራዉ በስልክ ያልቃል ወንጀል ለመፈፀም አንቺ እሱ እና ጌታሽ ብቻ የሚያቃቸዉ ብዙ የዚና መስሪያ ቦታዎች ምን ይሰራ ማን ይግባ ማን ይዉጣ የማይታይበት የወንጀል መስሪያ ቦታዎች በሁላችንም የመኖሪያ ሰፈሮች ቦታዎች እናገኛለን ፡፡  የሂክማ ነገር አላለቀም
                  #እስኪ #ፈገግ #እንበል
 .....አንዷ ሁሌ ላይብረሪ እያለች ትሄዳለች አቧቱ ሲጠይቃት ሁሌ ላይብረሪ እያለች ስታስቸግር ..አንድ ቀን አባቷ ማታ ስትመጣ በብትር ይገርፋታል የት ነዉ የምትሄጅዉ ??ሲሏት ላይብረሪ ስትል...አባቷ አልተማሩም ነበር ላይም ብረሪ ታችም ብረሪ የሄድሽበትን ብቻ ተናገሪ እንዳሉት አባት ትክክለኛ መሆን መቻል አለብን፡፡
 መቼም ቀን በቀን ይፈራረቃል አንድ ቀን ባሳለፍን ቁጥር ወደ ሽምግልና እየሄድን እና ወደ ሞት እየተጠጋን መሆኑን እረስተናል፡፡ እኛ ሞትን ብንረሳም ሞት ግን እኛን አይረሳም፡፡
ካልተሳፈሩበት ቶሎ ተሽቀዳድሞ
ጊዜ ታክሲ አይደለም አይጠብቅም ቁሞ
ተብሏል፡፡ ግን አሁን ጊዜ ሰዉ ታክሲ ተሰልፎ ይጠብቃል እንጂ ታክሲ ተሰልፎ ሰዉ መጠበቅ አቁሟል፡፡ ምን ለማለት ነዉ አንተም አንቺም እሱም እሷም ሞት ቁሞ እየጠበቀን ስለሆነ ጥርት ያለ ተዉበት አድርገን ሞትን እንጠብቀዉ፡፡

ነግቶ ፊርዶስ ጋር ተገናኘን ከበፊቱ በበለጠ ፍካቷ እየጨመረ ለኔ ያላት አመለካከት እየጨመረ ሄደ ፡፡ በቃ ምን ልበላችሁ እስከዛሬ በመደበቄ እኔ ስጨናነቅ እንደኖሩኩ አወኩኝ ቢሆንም አልሀምዱሊላህ አሁንም እፎይ ማለቱ በጣም ደስታ ፈጠረልኝ፡፡
ፊርዶስ እኛ ቤት እየመጣች አንድ ላይ እንሆናለን ፡፡

አንድ ቀን እናቴ ለፊርዶስ ምንድን ነዉ አታገቡም እንዴ ፊርዱ??? ሴት ልጅ ትዳር የሚያምረዉ በልጅነት ነዉ፡፡ እኔ ያገባሁት በ19 አመቴ ነዉ ፡፡ ከሁለት አንዳችሁ አግቡ እና በሰርጋችሁ እንልፋ አለቻት፡፡ ለፊርዶስ
..ፊርዱም ኢንሻ አላህ አይቀርም እኔ የማመቻቸዉ ስላለ ነዉ እንጂ በቤተሰብ የመጣልኝ አለ ታጭቻለሁ  ሆነም ቀረ የሂክማ ይቀድማል ተዘጋጂ አለች ሳቅ እያለች

https://telegram.me/mahbubil
18 views ⓵, 22:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-11 13:51:14

14 views ⓵, 10:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ