#አንድ_አፍታ ምክር ከጥበበኛው ሉቅማን ለልጁ #ምክር_2 #ልጄ_ሆይ ፧ ጥበብ (እውቀት ) ምስኪኖችን የነገስታት ደረጃ አድርሳለች፡፡ #ልጄ_ሆይ ፧ አደራህን በብድር ላይ ; ብድር የቀን ውርደት የማታ ጭንቀት ነው ፡፡ #ልጄ_ሆይ ፧ የማይረዳን ከማስረዳት ቋጥኝን ከቦታው ማንሳት ይቀላል ፡፡ #ልጄ_ሆይ ፧ ባወከው ነገር እስከምትሰራ ያላወከውን አትማር ፡፡ #ልጄ_ሆይ ፧ መጥፎ ጎረቤት ከከባድ ብረት በላይ ይከብዳል ;መራራ ነገሮችን ሁሉ ቀምሻለሁ ከድህነት በላይ መራራ ነገር አልቀመስኩም፡፡ #ልጄ_ሆይ ፧ አንድን ሰው ወንድም ለማድረግ ከፈለክ መጀመሪያ አስቆጣው በቁጣው ጊዜ ካለፍክ …ካልሆነ ተጠንቀቀው ፡፡ #ልጄ_ሆይ ፧ በሰው ቤት ውስጥ ከሆንክ አይንህን ጠብቅ፤ በስብስብ መካከል ከሆንክ ምላስክን ጠብቅ ፤ በሰላት ውስጥ ስትሆን ልብህን ጠብቅ ፡፡ " " የእብነ ከሲር ‘ቢዳያህ ወንኒሀያህ’ ከሚለው መፅሀፋቸው ውስጥ ከ40 በላይ የሉቅማን ምክሮች ተጠቅሰዋል ፡፡ ======= ሉቅማን ፡ ቁርዓን ውስጥ የተጠቀሰ በስሙም ምዕራፍ ያለው ፡ ነብዩ አለይሂ ሰላም ሰለሱ ” ☞አሰተሳሰቡ ሰፊ፣ ☞መልካም አሳቢ፣ ☞ዝምታን የሚያበዛ፣ ☞አላህን የሚወድ አላህም የወደደው ፣ ☞ጥበብም የቸረው ነው ” ብለውለታል ሉቅማን አፍሪካ ውስጥ ‘ኑባ’ የምትባል ቦታ የኖረ ሲሆን ‘ጦብሪያ’ የምትባል ቦታ እንደተቀበረ ይነገራል https://t.me/Alhamdumuredu https://t.me/Alhamdumuredu https://t.me/Alhamdumuredu 192 viewsIYl ዱስቱር, 11:04