Get Mystery Box with random crypto!

ልጆቼ በተለያየ ስም ይጠሩኛል:: ዳዲ: አባቴ:አባት... 'አባ' ብለው ሲጠሩኝ ግን: በቃ ምን ልበ | Albastros Ministries

ልጆቼ በተለያየ ስም ይጠሩኛል:: ዳዲ: አባቴ:አባት... "አባ" ብለው ሲጠሩኝ ግን: በቃ ምን ልበላችሁ ልቤ ይንሰፈሰፋል: ደስታዬ እጥፍ ይሆናል:: እኔ ሰው ሆኜ ይሄ ስሜት ከተሰማኝ እግዚአብሔር እማ እንዴት አብልጦ ደስስስ አይለው?

“ልጆችም ስለ ሆናችሁ እግዚአብሔር አባ አባት ብሎ የሚጮኽ የልጁን መንፈስ በልባችሁ ውስጥ ላከ።” ገላ4:6

ከዚህ ቃል የምረዳው: ሰጪው ራሱ እግዚአብሔር: እርሱን እራሱን የምጠራበት የልጁን/ የእየሱስን/ መንፈስ በልቤ ውስጥ ላከ:: አይገርማችሁም? እኔ ልጆቼ "ዳዲ ዳዲ" ሲሉኝ ባይከፋኝም አይጥመኝም እናማ አልፎ አልፎ "አባ" በሉኝ እላቸዋለው:: የሆነ በቃላት የማይገለፅ: የተለየ ስሜት /connection/ ይሰማኛል::

ደግሜ ልበላችሁ እኔ በልቤ ይሄ ከተሰማኝ... መለኮት የሆነውማ...

እስቲ ለሶሻል ሚድያ ያልሆነ: የእውነት አባትነቱ ገብቶን እና ተረድተን የልጁን መንፈስ በልቡ እንደፈሰሰለት ሰው በግላችን አባ አባ እንበለው:: ታድያ ይህን ያን አርግልኝ ለማለት ሳይሆን ደስስስስ እንዲለው:: ገላትያ 4:6