Get Mystery Box with random crypto!

ከኢንሳ የመጣ አዲስ መረጃ…! '…ዘመዴ እንደምንም ብለህ ይሄን መረጃ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት እ | Aki Man Z Menz

ከኢንሳ የመጣ አዲስ መረጃ…!

"…ዘመዴ እንደምንም ብለህ ይሄን መረጃ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት እና ለሕዝቡ አድርስ። መንግሥት በቅዱስ ሲኖዶስ አባቶች እና በአንተ ላይ ዶክመንተሪ እንዲሠራ አዟል። በአባቶች ላይ የውሸት ድምጽ ማስመሰል ሊሠራ ያቀደ ሲሆን ሲሠራም 2 ዋና ዋና ነገሮችን አስቦ ነው።

1ኛ፥ ለማኅበረሰቡ በውሸት እነዚህ አባቶች የፖለቲካ ንክኪ አጀንዳ እንዳሏቸው ለማስረዳት፥

2፥ የኦሮሞን ህዝብ እንደሰው እንደማይቆጥሩት የሚያሳይ ድምጽ ለማውጣት ነው።

"…በዚህም የታሰበው በማኅበረሰቡ ብቻ ሳይሆን የሲኖዶሱ አባቶች እርስ በእርሳቸው መተማመን እንዲያጡ ለማድረግ የታሰበ ነው። እናም ስልክ ደግሞ 100% በኢትዮቴሌኮም የፎቶጋለሪ ሳይቀር መመልከት ይችላሉ። እንዲህ መጠቀም ከጀመሩ 1 አመት አልፏቸዋል።

"…የInsa cyber security specialist ከሰለሞን ሶካ የ insa director encrypted መልዕክት ተልኳል። ይህም የቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት አባቶች እንዲሁም የሃይማኖት ተቆርቋሪዎች accounts check እንዲያደረጉ፣ እንቅስቃሴያቸው እንዲጠና፣ እንዲሁም የማኅበረሰብ አንቂዎች ጭምር እንዲበረበር፣ ከዚያውስጥ ደግሞ ዘመዴ ላይ Documentary ለመሥራት Vulnerability እየፈለጉ ነው። በቅርቡም በአቡነ ማቲያስና በአቡነ አብርሃም ላይ የተሠራ voice over ለማኅበረሰቡ ለማውጣት በዝግጅት ላይ ናቸው።

"…በቀደም ዕለት በእነ አካለወልድ የተሰጠው መግለጫ ተመልክቶ ከመግለጫው በፊት እነ ሽመልስ አብዲሳ የነገሯቸው ነገር "እኛ ውስጥ ውስጡን እንጨርሰዋለን እናንተ ግን ግፉበት። ወደ ኋላ የሚል በህይወቱ ላይ እንደፈረደ ይቁጠር። አንዴ ገብተንበታል ዳር ሳናደርስ አንመለስም። የብልፅግናን ፈጥረን ወደ አራት ኪሎ የመጣነው በዚሁ መንገድ ነው። አዲሲቱን ኦሮሚያ ለመፍጠር በሚደረገው ሂደት ላይ የእናንተ ድርሻ ቀላል አይደለም። በርቱ ነበር ያላቸው። ከኢትዮጵያ ጋር አብሮ መኖር ካልተቻለ ዐማራን ለትግሬና ለሱዳን ሰጥተን፣ ሱማሌ ወደ ፈለገበት እንዲሄድ አድርገን፣ ደቡብን ከእኛ ጋር ቀላቅለን በኃይ ግማሽ ደቡብ ወሎን እና አዲስ አበባን ጨምሮ ይዘን መገንጠል ነው።" ይሄ ሕገ መንግሥታዊ መብታችን ነው። ማንም አያስቆመንም። ምንም አትስጉ ነው ያላቸው። መነኩሴዎቹ አሁን ታግተው ነው ያሉት።

"…ዘመዴ Voice over ን በተመለከተ እንደምንም ብለህ ለቅዱስ ሲኖዶሱም ለኅበረተሰቡም ቀድመህ ማድረስ አለብህ። መንግሥት ቅዱስ ሲኖዶሱን ከህዝቡ ለመነጠል እንደ ዋነኛ መንገድ ነው ሊጠቀመው ያሰበው። ይህም ስል የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት አባቶች በኩራት እንዳይቃወሙት አንገት ማስደፊያ ነው። መረጃው ቀድሞ ከወጣ የጨጓራ በሽተኞች ከመሆን በዘለለ ምንም አባታቸው አያመጡም። የሚገርምህ እኔ ሃይማኖቴ አይደለም። ነገር ግን ሰዎቹ ሊፈጥሩ ያሰቡት ምስቅልቅል ስላሳሰበኝ ነው። በአሁን ወቅት ደግሞ በጣም የምት ሰማው እና ታማኝ የመረጃ ምንጭ ስለሆንክ ብዬ ነው ወዳንተ መምጣቴ።

"…በአጠቃላይ ስለዚህ ሥራ የሚያውቁ ሰዎች 3 የኮምፒዩተር ስፔሻሊስቶች፣ አንድ ስሙን ከሰሞኑ ስሙን የምነግርህ አርቲስት የድምጽ የአባቶችን ድምፅ የማስመሰሉን ሥራ እንዲሠራ ተመርጧል። አርቲስቱን በፎቶ እሰጥሃለሁ። አርቲስቱ ያስመሰለውን የአባቶች ድምጽ ወደ ኮምፒዩተራቸው አስገብተው ነው በስልክ እንደተነጋገሩ የሚያስመስሉት። ንግግሩ ኦሮሞን የሚያንቋሽሽ አድርገው እንዲሠራ ነው የታዘዘው። ድምፁ ከተሠራ በኋላ አርቲስቱ ይገደላል ወይ መርፌ ወግተው ያጀዝቡታልም ተብሏል። አዛዡ ሰለሞን ሶካ እና ከሱ በላይ ያሉ ሰዎች ናቸው።

"…አንተን በተመለከተ ኢንተርኔት ላይ ባለህ እንቅስቃሴ የተውካቸውን ኮቴዎች ተከተለው አካውንት መጥለፍ ሲሆን፣ በዚያም ሳታውቅባቸው የሚችሉትን ያህል መረጃ መውሰድ ነው። ካልቻሉ ደግሞ ሶሻል enginering የሚባለውም ቴክኒክ በመጠቀም ነው ሊመጡብህ ያሰቡት። በዚህም ወዳጅ መስለዉ መረጃው መመዝበር ነው። ከዛ በራስህ መረጃ documentary ሠርተው ያንተ ተከታዮች ላይ conspiracy መፍጠር። ይሄን ካሳካን ቢያንስ እንደ ጉድ ከሚከተሉህ ሰዎች ከብዙ ሚልዮኖቹ ቢያንስ ግማሽ የሚሆነው ሰው ከአንተ መራቅ ነው የፈለጉት።

"…ያንተከትሎ ከዚያ በኋላ በዋና ዋና መገናኛ ብዙሃን ሚዲያዎች የሠሩትን documentary አንተን ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንደ አሸባሪ ማሳየት ነው የፈለጉት። በዚህም ዋና ዓላማው አንተን በወንጀለኛ፣ በዘር አጥፊነት ለመፈረጅ ነው። ጭቅጭቅ ነበረባቸው። ልጁ ለዚህ ፍረጃ አይመችም የሚል ነገር ተነሥቶም ነበር። ነገርግን አቶ ሰሎሞን ሶካ ይገባናል ነገርግን ሌላ የተሻለ ምርጫ የለንም ስለዚህ በዚሁ ግፉበት የሚል መመሪያ ሰጥቷቸዋል።

"…ዛሬ voice over እንዲሰሩ ከታዙት መካከል ከinsa ፕሮጀክቶች በሙሉ ወደ እኛ ወደ ኦሮምያ ደኅንነት ቢሮ እንዲመጡ ተደርጓል። በኦሮሚያ ደህንነት ቢሮ እንዲሠራ የተፈለገው አቶ ተመስገን በሚሠራው የደኅንነት ቢሮ መተማመን በማጣታቸውና ዐማሮቹ እንደ ፓርቲም፣ እንደ ክልልም ለእኛ ለኦሮሚያ ብልጽግና የሚያሳዩት እንቅስቃሴ እጅግ መተማመን ስለጠፋበት ነው። አቶ ደመቀ ከእነ አቢይ ያፈነገጠ ይመስለኛል። አቶ ተመስገንም በጎጃሜዎቹ የተጠለፈ ነው ብለው አያምኑትም። በመከላከያውም ስንጥቃት አለ። የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ በአባቶች ጥበብ አለፈ እንጂ ከህዝቡ ይልቅ ጦሩ ነበር የሚፋጀው።

"…በኦሮሚያ ደኅንነት ቢሮ የሚሠሩት ከቱርክ ተምረው የመጡ እንዲሁም የቀድሞ insa ላይ የነበሩ ሰዎች ናቸው። አንተ አሁን መረጃውን ለማኅበረሰቡ እና ለቅዱስ ሲኖዶሱ አሳውቅ። ዘመዴ ፍጠን ትናንት ምሳ ሰዓት ላይ ሙሉ ለሙሉ ፕሮጀክቶቹን በአጠቃላይ ወደ እኛ ኦሮሚያ ደህንነት ቢሮ መጥቷል። ሁሉም ያነቡሃል። ግትርነትህን፣ ሃቅህን ይወዱታል፣ እልህህ ደስስ ይላቸዋል። የሚጠሉት ሴራቸውን ስለምታፈራርሰው ነው። በፊት በፊት ጓደኛህ ስለሆነ ዳንኤል ክብረት ነው መረጃ የሚሰጠው ብለው ይሟገቱ ነበር። አሁን አሁን ግን በተለይ ዳንኤል ላይ ከጻፍክ በኋላ ስለ ዳንኤል እንደ አዲስ መረጃ ካንተ ስላገኙ በአንተ ላይ ክትትልና የመረጃ ምንጮችህን ለማወቅ እንቅልፍ አጥተዋል። ነገር ግን ምንም ዱካ ሊያገኙ አልቻሉም። የአንስ ልዩ ነው። በርታ ዘመዴ። ህዝቡ አስቀድሞ ተጠንቅቆ እንዲጠብቅ አንተ ይሄን ቀድመህ አውጣሁ።

"…ስላለኝ አውጥቼዋለሁ። እኔን በተመለከተ ግን በ email የምጻጻፈው ከጀርመን መንግሥት ለሥራ ጉዳዮች ብቻ ነው። ለማንም በኢሜል መልስ ሰጥቼ አላውቅም። ሲበረብሩ ውለው ቢያድሩ የሚጣሉት ከጀርመን መንግሥት ጋር ነው። በተረፈ በስልኬ ላይ የሚቀመጥ ምንም የተለየ ነገር የለኝም። የማገኛቸውን መረጃዎች ሃገር የሚያፈርሱትን በመደበቅ ነው በስሱ እንዲደነግጡ፣ ንስሀም እንዲገቡ የምለቅላቸው። የብዙዎቹን ነውር ሁላ ደብቄያለሁ። እነሱ አሸባሪ ሲሉኝ እኔ ደግሞ እየቀፈፈኝ ገመድ ፈልገው ይታነቁ ዘንድ የሚያደርጋቸው መረጃዎችንም እለቃለሁ።

"…ቆይቼ የአስተያየት መስጫ ሰንዱቁን እከፍትላችኋለሁ።