Get Mystery Box with random crypto!

'ተባለ...ተባለ እንዴ' ------ ፀሐዬ ዮሐንስ፣ ተመስገን ተካ እና ሮሃ ባንድ አስገራሚ ጥምረት | AfandishaHarar 🇪🇷🇪🇹🇯🇴🇸🇩🇪🇭🇸🇴

"ተባለ...ተባለ እንዴ"
------
ፀሐዬ ዮሐንስ፣ ተመስገን ተካ እና ሮሃ ባንድ አስገራሚ ጥምረት ያሳዩበት አልበም።
----
አወይ ሰሞኑን ምን ነካህ
ጸባይህ ተቀይሯል።
(እስቲ እኔን ለቀቅ አርጉኝ)
አወይ ሰሞኑን ስላንተ መክሳትህ
መጥቆርህ ብዙ ይወራል።
(እንዲህም ተባለ እንዴ?)
ተባለ (ተባለ እንዴ?)
ተባለ (ተባለ እንዴ?)
----
"ተባለ...ተባለ እንዴ?" ከዚህ አልበም መውጣት በፊት ተደጋግሞ የማይነገር ሐረግ ነበር። ይህ አልበም እንደወጣ ግን ወጣቶችና ጎልማሶች እንደ ፋሽን የሚናገሩት የመግባቢያ ቋንቋ ሆኗል።

ይህ አልበም በ1982 ነው የወጣው። በዚህ አልበም የተነሳ የፀሐዬ ዮሐንስ ዝና በጣም ነው የጨመረው። ታዋቂው ሮሃ ባንድም የሙዚቃ እጀባውን በልዩ ቀለም በመወጣቱ በጣም የተደነቀው። ከማንም በላይ በዚህ ስራ ልዩ ብቃቱን ያሳየው ግን ወጣቱ ገጣሚ ተመስገን ተካ ነው።

ተመስገን ተካ በዚያ ወቅት ገና የ24/25 ዓመት ወጣት ነበር። ከዚህ ስራ በፊት ለተለያዩ አርቲስቶች የዘፈን ግጥሞችን ሰጥቷል። በተለይ ለኬኔዲ መንገሻ በሚጽፋቸው ግጥሞች መደነቅ ጀምሯል። ለሙሉ አልበም ግጥም መጻፍ የጀመረው ግን በዚህ የፀሐዬ ዮሐንስ ካሴት ላይ ነው።
-----
ተመስገን ተካ ለረጅም ጊዜ በሕይወት መቆየት ካልቻሉትና ቦግ ብለው ከጠፉብን የጥበብ ከዋክብቶች አንዱ ነው። በ1993 ገና በለጋ ዕድሜው ተቀጭቷል።
RIP Temesgen Teka.
ተባለ....ተባለ እንዴ?
ተባለ...ተባለ እንዴ?