Get Mystery Box with random crypto!

Guzo Adwa updates

የቴሌግራም ቻናል አርማ adwav — Guzo Adwa updates G
የቴሌግራም ቻናል አርማ adwav — Guzo Adwa updates
የሰርጥ አድራሻ: @adwav
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.98K
የሰርጥ መግለጫ

https://t.me/adwav

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 14:55:01 የዓመቱ የመጨረሻ ጉዟችን ወደ ''እንሳሮ''  ይሆናል።
                        27ኛ ጉዞ

የፊታችን እሁድ (ነሀሴ 29) ከአዲስ አበባ 135 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ወደሚገኘው እና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ተወዳጅነት ወዳተረፈው የእንሳሮ ውብ መልክዓምድር ፣ ፏፏቴዎች እና ዋሻዎች  አዝናኝ የእግር ጉዞ እናደርጋለን።

በፍፁም እንዳያመልጣችሁ!!

የጉዞ ዓይነት :- ከጀማሪ  እስከ ከፍተኛ ልምድ ተጓዦች ሁሉ የሚሆን።

በዚህ ጉዞ ለመሳተፍ የሚጠየቀው አጠቃላይ የጉዞ መዋጮ 1099 ብር ብቻ ነው።

የጉዞ መዋጮው የሚያካትተው ( ደርሶ መልስ ትራንስፖርት ፣ ቁርስ ፣ በባለሙያ የተዘጋጀ ትኩስ ምሳ ፣ ሻይ ቡና ፣ በጉዞ ወቅት የሚበሉ ቀለል ያሉ ምግቦች ፣ የታሸጉ ውሃዎች ፣ የመግቢያ እና የአስጎብኚ ክፍያዎችን ጨምሮ ።

በዚህ ጉዞ ተሳታፊ ለመሆን እርግጠኛ ብቻ ሲሆኑ

ለምዝገባ

በነዚህ ስልክ ቁጥሮች ፈጥነው ይደውሉ!   ፣ +251942545470 ፣ +251964423971 አልያም   በ @guzoadwahiking @guzoad @miki_2012 አጭር የፅሁፍ መልዕክት ይላኩልን ።

መልካም  የስራ ቀን  !!
ሰላም ለሀገራችን

#ethiopia #landoforigins  #guzoadwahiking #ensaro
616 viewsedited  11:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 14:55:00
552 views11:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 00:59:08
መስከረም 8 2015 ዓ.ም ከተጨማሪ ውብ ዝግጅቶች ጋር ኮረማሽ ላይ ዳግመኛ አንገናኝም ወይ ???

ሌላ ቀጠሮ መያዝ ክልክል ነው!!

ምዝገባው በጥቂት ቀናት ውስጥ ይጀመራል።

ሠላም ለሀገራችን !!
1.0K viewsedited  21:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 23:35:00 Guzo Adwa updates pinned a video
20:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 17:11:51 ባሳለፍነው እሁድ ወደ አንጎለላ ተጉዘን ነበር

ነሐሴ 22 ቀን 2014 ዓ.ም
አንጎለላ / እንቁላል ኮሶ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘ ኢትዮጵያ
በቀድሞው ሸዋ ክፍለ አገር ተጉለት እና ቡልጋ አውራጃ
አንጎለላ ቀበሌ ልዩ ቦታው እንቁላል ኮሶ በተባለ መንደር  ከእናታቸው ወ/ሮ እጅጋየሁ ለማ እና ከአባታቸው ኃይለ መለኮት ሣህለሥላሴ ነሐሴ 12 በዕለተ ቅዳሜ 1836 ዓ.ም  ተወለዱ።

በዚህችው ቀን ከ4 አመታት ቀድም ብሎ የኋላዋ ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ ተወልደውባታለችና፤ ነሐሴ 12 ቀን ታሪካዊ ግጥምጥም አላት።

በተመሳሳይ መልኩ በፈረስ ስማቸው አባ ጎራው በመባል የሚታወቁት በዓድዋ ጦርነት እና ከዛም  ቀደም ብሎ  ከኢጣሊያ ጋር በተደረጉ የአምባላጌ እና የመቀሌ ጦርነቶች ላይ በጀግንነት የተዋጉ እና ድል ያደረጉ የጦሩ መሪ ጀግናው ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦም ተወልደውባታል።

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ እና ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ በተመሳሳይ ቀን በተመሳሳይ ዓመት በአንጎለላ ተወልደው በተመሳሳይ ቀን በጥንታዊው የአንጎለላ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ተነስተዋል። (አንጎለላ ኪዳነምህረት የሄደ ሰው በዓድዋ የወደቀው የጀግናው ፊታውራሪ ገበየው ክቡር አስክሬን በመስታወት ሳጥን ውስጥ ኾኖ ማየት ይችላል)

እንዳለፉት ጥቂት የማይባሉ ዓመታት ሁሉ ዘንድሮም ከነሐሴ 12 ጀምሮ በተለያዩ ሁነቶች ጀግኖቻችን በክብር ያስረከቡልንን አገር ለማጽናት አደራቸው ማሰብ ይረዳን ዘንድ ልደታቸውን ምክንያት አድርገን ቀናቱን ስንዘክር ቆይተን ደማቁን መዝጊያ በትውልድ መንደራቸው በማድረግ አጠናቀናል።

በጉዟችን ከ ሶስት ኪሎ ሜትር  ያልበለጠ የእግር ጉዞ በአንጎለላ የገጠር መንደሮች ውስጥ አድርገናል።  በዘመኑ አጠራር በሰሜን ሸዋ አስተዳደር ዞን ውስጥ ከሚገኙ ወረዳዎች አንዱ በሆነው ባሶና ወራና ወረዳ አንጎለላ ቀበሌ ውስጥ ወደ ምትገኘው እና በአጼ ናዖድ ዘመነ መንግስት በ1487 ዓ/ም በተገደመችው ጥንታዊቷ አንጎለላ ጽርሐ አርያም ሰሚነሽ ኪዳነ ምህረት ገዳምን ጎብኝተናል። 

ከገዳሙ  በስተ ምዕራብ ቀረብ ብሎ የሚገኘው ለዘመናት ተቀበሮ የቆየው እና በጉዞ ዓድዋ ግንባር ቀደምነት ከፍተኛ ውትወታ ተደርጎበት ጥበቃ እንዲያገኝና የተቀበረው ቤተመንግስት በቁፋሮ የማውጣት ስራው የተጀመረው በሙያተኞች የመካከለኛው ዘመን ሥነ- ሕንጻ መኾኑ የሚታምነና   የአካባቢው ማሕበረሰብ በተለምዶ የንጉስ ሳህለ ሥላሴ ቤተ መንግስትንም እያለ የሚጠራውን ቦታ ዘንድሮም ጎብኝተናል።

ይህንን ቤተ መንግስት ከተቀበረበት እስከ መጨረሻው የማውጣቱ ስራና ቦታውን ይበልጥ ለሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ቱሪስቶች ለጉብኝትም ይሁን ለጥናት እና ምርምር  ምቹ የማድረግ ስራው ከአመት አመት ከመሻሻል ይልቅ እንደውም በዚያው ተዳፍኖ ስራ መቆሙን ዳግም ታዝበናል።

በዚህ ጉዞ የክብር እንግዳችን የነበሩት የኢትዮጵያ ቅርስ ባላደራ ማኅበር ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መቆያ ማሞ በዕለቱ የነበረንን ትዝብት ተጋርተውናልና፤ በቀጣይ  ከሚመለከታቸው ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር ለችግሩ  አንድ መፍትሔ ያመጣሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን።

በመጨረሻም በደማቅ ሀገርኛ  ድግስ ተቀብሎ ፣ ተንከባክቦ እና መርቆ የሸኘንን ወዳጃችንን ወርቅአገኘው  ገ/ማሪያም  እንዲሁም የዚህ ጉዞ ድምቀት ለነበራችሁ የታሪክ እና የጉዞ ወዳጅ ቤተሰቦቻችን ከልብ ለማመስገን እንወዳለን።
__

የጉዞ ዓድዋ ሃይኪንግ የዓመቱ የመጨረሻ ጉዟችን የፊታችን እሁድ (ነሀሴ 29) ወደ ተወዳጁ ''እንሳሮ''
ይካሄዳል።

ውስን ቦታዎች ብቻ ስለሚቀሩን በተከታዮቹ አድራሻዎች ፈጥነው  ይደውሉ
+251942545470 ፣ +251964423971
ወይንም  @guzoadwahiking @guzoad @miki_2012 አጭር የፅሁፍ መልዕክት ይላኩልን ።

#guzoadwahiking #ethiopia #landoforigins #angolela #semienshewa #dagmawimeneliek #guzoadwa
1.2K viewsedited  14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 17:11:25
803 views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 11:53:53
የጉዞ ዓድዋ ሃይኪንግ ቡድን የክረምቱም ፣ የዓመቱም የመጨረሻ ጉዞ '' እንሳሮ''  ይሆናል።

እሁድ (ነሀሴ 29)

በዚህ ጉዞ ለመሳተፍ የሚጠየቀው አጠቃላይ የጉዞ መዋጮ 1099 ብር ብቻ ነው።

የጉዞ መዋጮው የሚያካትተው ( ደርሶ መልስ ትራንስፖርት ፣ ቁርስ ፣ በባለሙያ የተዘጋጀ ትኩስ ምሳ ፣ ሻይ ቡና ፣ በጉዞ ወቅት የሚበሉ ቀለል ያሉ ምግቦች ፣ የታሸጉ ውሃዎች ፣ የመግቢያ እና የአስጎብኚ ክፍያዎችን ጨምሮ ።

በዚህ ጉዞ ተሳታፊ ለመሆን እርግጠኛ ብቻ ሲሆኑ

ለምዝገባ

በነዚህ ስልክ ቁጥሮች ፈጥነው ይደውሉ!  +251964423971 ፣ +251942545470 አልያም  @guzoadwahiking ፣ @guzoad  ወይንም በ @miki_2012
አጭር የፅሁፍ መልዕክት ይላኩልን ።


ማሳሰቢያ!!

የነገው ''የአንጎለላ'' ጉዞ ምዝገባ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቋል ::

አርፍደው ክፍያ የሚፈፅሙ ተጓዦች ካሉ ገንዘብ ተመላሽ ይደረጋል ወይንም ለቀጣዩ ጉዞ ይተላለፋል።

መልካም የዕረፍት ቀናት ይሁንልን!!
ሰላም ለሀገራችን
1.1K viewsedited  08:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 07:27:15 ጉዞ አንጎለላ
ሁለት ቀናት ብቻ !!

የፊታችን እሁድ ነሀሴ 22

የመጨረሻው መኪና ለ 8 ተጓዦች ብቻ  የሚሆን ቦታ ቀርቶታል።

ከዚህ ማሳሰቢያ በኋላ  ፈጥነው  ክፍያ የሚፈፅሙ 8 ተጓዦች ብቻ ከእኛ ጋር የመጓዝ ዕድሉን ያገኛሉ።

ይህ በአይነቱ  ልዩ  የሆነ ታሪካዊ ጉዞ  የእምዬ ምንሊክ እና የእቴጌ ጣይቱን ልደት በማስመልከት
በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ  የሚካሄድ ነውና በፍፁም አያምልጣችሁ።

ለማንኛውም አይነት ጥቆማ እና የጉዞ ምዝገባ እነዚህን  የቴሌግራም አድራሻዎች ብቻ ይጠቀሙ  @guzoadwahiking , @guzoad ,@miki_2012

አልያም በ  +251942545470 ፣ +251964423971
ይደውሉልን ።

አርፍደው ክፍያ ለሚፈፅሙ ተጓዦች ክፍያ ተመላሽ ይደረጋል ወይንም ለቀጣዩ ጉዞ ይተላለፋል።

መልካም ቀን !!
1.4K views04:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 07:27:10
1.3K views04:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 07:27:09
1.3K views04:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ