በአሜሪካ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በረዶ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ ጣለ!
በሀገሪቱ ምስራቃዊ ባህር ዳርቻ ለሁለት ተከታታይ ቀናት በረዶ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ ጥሏል።
በኒውዮርክ ፣ ኒውጀርሲና ፔንሲልቫኒያ መጣል የጀመረው ይህ ከባድ ዝናብ በረራዎችን እያስተጓጐለ ሲሆን ፤ የኮቪድ-19 ክትባት የሚሰጡ ስፍራዎችም እንዲዘጉ አድርጓል።
የኒውዮርክ ከተማ ከንቲባው ቢል ዴ ብላሲዮ አስገዳጅ እስካልሆነ ድረስ በሚል የጉዞ ክልከላዎችን አስተላልፈዋል።
ሁኔታው ከዚህ የከፋ እንዳይሆን መስጋታቸውንም ተናግረዋል።
የኒውጀርሲ አስተዳዳሪ ፊሊፕ መርፊ በተመሳሳይ መንገዶች እንዲዘጉ አድርገዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ከአማካሪዎቻቸው ጋር ስለመምከራቸውም የቢቢሲ ዘገባ ያሳያል።
(ብስራት ራዲዮ)
@admasradio