2022-07-12 19:20:49
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ፍርድ ቤት ቀርበው በሜ/ጀ ክንፈ ዳኘው የዕርሻ መሳሪያና የመርከብ ግዢን ክስ ክስ ላይ የመከላከያ ምስክርነት ቃላቸውን ሰጡ።
አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ቀርበው ሜጀር ጀነራል ክንፈ ዳኘው በተከሰሱበት የዕርሻ መሳሪያና የመርከብ ግዢ ሙስና ክስ ላይ በተቆጠሩበት የመከላከያ ምስክርነት በዕውነት ለመመስከር ቃለ መኃላ ፈጽመው ነው የመከላከያ ምስክርነት ቃላቸውን የሰጡት።
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ የፍትህ ስርዓቱን አክብረው የመከላከያ ምስክርነታቸውን ቃላቸውን ለመስጠት ፍርድ ቤት በመቅረባቸው ከችሎቱ ዳኞች እና ከሜ/ጀ ክንፈ ጠበቆች ሀፍቶም ከሰተና ከዘረሰናይ ምስግና እንዲሁም ከዓቃቢህግ ጌታሁን ተሰማ በኩል ከፍ ያለ ክብርና ምስጋናና ተችሯቸዋል።
ቃለ መኃላ ከፈጸሙ በኋላ በጠበቆች በኩል አቶ ሀይለማርያም መከላከያ ምስክርነታቸው እንዲሰማ የተፈለገው ጭብጥ ለችሎቱ ተመዝግቧል።
ጠበቆቹ በቀዳሚነት ሜ/ጀ ክንፈ ዳኘው የተከሰሱበት በዕርሻ መሳሪያ ግዢን በተመለከተ የብረታብረትና ኢንጂነሪግና ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ለማቋቋም ያስፈለገበት አስረጂ ምክንያቱ ምን እንደሆነ :የትራክተር (የዕርሻ መሳሪያ) በከፊልና በሙሉ ተገጣጣሚ አካላትን እንዲገዛ የተደረገበትን : ሜቴክ የዕርሻ መሳሪያ ለገበሬዎች ሊያቀርብ የፈለገበትን ምክንያት : ፖሊሲው ምን እንደነበር የቴክኖሎጂው ሽግግርን በተመለከተ ሜቴክ እንዲሰራ የተፈለገበትን ምክንያት :በአጋርነት መርህ ላይ ተመስርቶ የሚሰራው አሰራር ከየትኛው ፖሊሲ የመጣ እንደሆነ እና ቴክኖሎጂ በጨረታ የሚገዛበትን ሁኔታን እንዲሁም በኛ ሀገር ደረጃ ቴክኖሎጂ የሚገዛበትን ሂደትን በተጨማሪም ሜቴክ በተቋቋመበት አዋጅና ደንብ መሰረት የሚነሳበት ቅሬታና ችግር ሲኖር ለመፍታት በምን መልኩ አቅጣጫ ተሰቶ እንዲፈታ እንደሚደረግ ገልጸው እንሰዲያስረዱላቸው ጠበቃ ዘረሰናይና ሀፍቶም ጭብጣቸውን አስመዝግበዋል።
አቶ ሀይለማርያምም በተያዘው ጭብጥ መነሻ ከጠበቆች የተነሳላቸውን ዋና ጥያቄ ላይ የመከላከያ ምስክርነታቸው ቃልን ሰተዋል።
አቶ ሀይለማርያም በነበሩበት የሀገር መሪ ሀላፊነት ወቅት በሜቴክ ጉብኝት ካደረጉ በኋላ የታዩ ጉድለቶች እንዲስተካከሉ የሰጡት አቅጣጫ አላስታውስም ማለታቸውን ተከትሎ ማስታወስ እንዲያስችል ተብሎ በወቅቱ አቶ ሀይለማርያም ከጉብኝት በኋላ ያደረጉትን ውይይትና የተሰጠ አቅጣጫን በተመለከተ በጠበቆች በመከላከያ ማስረጃ የተመዘገበ ቪዲዮን በላፕቶፕ ኮምፒዩተር ለ3 ደቂቃ እንዲመለከቱ ተደርጓል።
በጠበቆች የቀረበ ዋና ጥያቄ ከተጠናቀቀ በኃላ የዓቃቢህግ መስቀለኛ ጥያቄ በተጨማሪም የፍርድ ቤቱን ለተነሳ የማጣሪያ ጥያቄ ላይ አቶ ሀይለማርያም መልስ ሰተዋል።
የዕርሻ መሳሪያ የመከላከያ ምስክርነት ከተጠናቀቀ በኋላ የችሎቱ ዳኞች አቶ ሀይለማርያምን ለ5 ደቂቃ በመኪናቸው ውስጥ እንዲያርፉ አድርገዋል።
ከአምስት ደቂቃ በኋላ ደግሞ በመርከብ ግዢ ክስ ላይ የመከላከያ ምስክርነት ቃላቸው ተሰምቷል።
በመርከብ ግዢን በተመለከተ የሜ/ጀ ክንፈ ዳኘው ጠበቆች ጭብጣቸውን አሲዘዋል።
የአባይና ህዳሴ መርከቦች በመንግስት ውሳኔ ግዢው እንዲፈጸም ከተደረገ በኋላ መርከቦችን ማስተዳደር ጋር በተያያዘ ከኢትዮጲያ ባህር ትራንዚት ጋር እና ከማሪታይም ጋር የነበረ ሰጣ ገባ በተመለከተ ለጠ/ሚኒስትሩ ይጻፍ የነበረ ደብዳቤ ስለመኖሩ ማረጋገጫ ጥያቄ እና መርከቡን አሰርቶ ለማንቀሳቀስ ወይም በስክራፕ ቆርጦ ለማንቀሳቀስ የነበረው ችግርን መንግስት መፍትሄ እንዲሰጥበት ለጠ/ሚ የተጻፈ ደብዳቤ ስለመኖሩ እንዲሁም መርከቦቹ ተገዝተው ከተጠገኑ በኋላ ማሪታይም ከመንግስት አቅጣጫ ካልተቀመጠ ፍቃድ አልሰጥም ማለቱን ተከትሎ ለአቶ ሀይለማርያም የተጻፈ ደብዳቤ መኖሩ ወይም አለመኖሩን እንዲያስረዱላቸው እንደሚፈልጉ ገልጸው ጭብጥ አስመዝግበዋል።
በዚህ ጭብጥ መነሻ ከጠበቆች በቀረበላቸው ዋና ጥያቄ የመከላከያ ምስክርነት ቃላቸውን ሰተዋል።
በወቅቱ የተጻፈ ደብዳቤ እንዳልደረሳቸው የሰጡትን ቃል ተከትሎ በችሎቱ ፍቃድ መሰረት በመንግስት የመፍትሄ አቅጣጫ እንዲሰጥ ከባህር ትራንዚት በጥር 16 ቀን 2006 ዓ/ም ከሜሪታይም ደግሞ ጥቅምት 1ቀን 2006 ዓ/ም የተጻፈ ደብዳቤ በችሎት ቀርቦ እንዲመለከቱ ተደርጓል። ከጠበቃ የተነሳላቸውን ዋና ጥያቄ ካጠናቀቁ በኋላ የዓቃቢህ መስቀለኛ ጥያቄ ሆነ የፍርድ ቤቱ የማጣሪያ ጥያቄ አልቀረበላቸውም።
አቶ ሀይለማርያም በዕርሻ መሳሪያም ሆነ በመርከብ ግዢ ጉዳይ የሰጡት መከላከያ ምስክርነት ቃል ከድምፀ መቅረጫ ወደ ጽሁፍ እንዲገለበጥ ፍርድ ቤቱ አዟል።
አቶ ሀይለማርያም የፍትህ ስርዓቱን አክብረው ፍርድ ቤት መቅረባቸው የዳኝነት ሂደቱን ለመታዘብ እንደሚያስችላቸው የችሎቱ ዳኞች ገልጸው አመስግነዋቸዋል።
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት
SHARE & JOIN
@Adis_Neger_Ethio
@Adis_Neger_Ethio
89 viewsedited 16:20