Get Mystery Box with random crypto!

የቡና ቅምሻ ዉድድር አለመካሄዱ ቡና አምራችና አቅራቢዎችን ለኪሳራ ዳርጓል በኢትዮጵያ ለ3 ተከታታ | አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe

የቡና ቅምሻ ዉድድር አለመካሄዱ ቡና አምራችና አቅራቢዎችን ለኪሳራ ዳርጓል

በኢትዮጵያ ለ3 ተከታታይ ዓመታት ሲካሄድ የነበረዉ የባለ ልዩ ጣዕም ቡና ቅምሻ ዉድድር ( ካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ) በዘንድሮው ዓመት እንደማይካሄድ የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣንን ማስታወቁን ተከትሎ በግዢ እና በቅድሚያ ዝግጅት ወቅት ባለመነገሩ ለከፍተኛ ኪሳራ መጋለጣቸዉን ቡና አምራች አርሶአደሮችና አቅራቢዎች ለአዲስ ዘይቤ ገልጸዋል።

በ2015 ዓ.ም መጨረሻ ለሚካሄደው ውድድር ከፍተኛ መጠን ያለዉ ቡና ያዘጋጁት አርሶአደሮች እና ወደ ላኪዎች የሚያቀርቡ የግል ቡና ሳይት ባለቤቶች ካፕ ኦፍ ኤክስለንስ ከመምጣቱ በፊት ከአርሶአደሩ በአማካኝ ከ20 እስከ 30 ብር ይገዙ የነበረውን 1 ኪሎ እሽት ቡና በዚህ አመት እስከ 90 ብር ግዥ መፈጸማቸውን አስረድተዋል።

በሲዳማ ክልል በአርቤጎና የሚገኘው ሲፋሙ የተባለው የግል ሳይት "ለ4ኛ ጊዜ ለሚካሄደው የቡና ጥራት ዉድድር ከ11 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ግዢ መፈፀሙንና ውድድሩ ሲቀር እስከ 4 ሚሊዮን ብር ኪሳራ እንደሚደርስበት ስጋቱን አስፍሯለ፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/hawassa/current-affairs-am/failure-to-hold-the-coffee-tasting-competition-has-led-to-losses-for-coffee-producers-and-suppliers